May 17, 2012

በጠራ ጨረቃ»



በጠራ ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
አይኖቿ እያበሩ እንደ ከዋክብት
«ሳማት ! ሳማት !» አሉት
«እቀፍ ! እቀፋት።»
አላወላወለም ወጣቱ ታዘዘ
ወገቧን አንገቷን እጇን በእጁ ያዘ
ምንም እንኳ ጡቷ እንደሾህ ቢዋጋ
ጣቷ በመሆኑ የጉማሬ አለንጋ
ጆሮ ግንዱን ሰማው በጥፊ ሲናጋ።
ዋ ጀማሪ መሆን ! ዋ ተማሪነት
ዋ ትእዛዝ መፈጸም ዋ ምክር መስማት !
በጠራ ጨረቃ በኩለ ሌሊት...

መንግስቱ ለማ

No comments:

Post a Comment