May 17, 2012

እውነት ለፈለገ....



ፀሀይ ስትገባ
ጥያቄ ይወጣል ፀሀይን ተክቶ
ልቤም እስከንጋት ያልፈዋል ተኝቶ
ግድ ነው በለሊት አዳፍኖ ማለፉ
እሳትን ባመድ ሆድ ጥያቄን በን'ቅልፉ
ከጎረምሶች ከንፈር ጪስ እየነጠቀ
ከኮረዶች ጡት ላይ ሽቶ እየሰረቀ
ነፋሱ ይዞራል
ግና በምላሹ ምስጢር መች ይነግራል
መስኮቴን ብከፍተው
በብርድ ልብሴ ላይ ኮከቦች ፈሰሱ
እውነትለፈለገ ውበት ነው ወይ መልሱ

(በእውቀቱ ስዩም)

No comments:

Post a Comment