ልጅነት ሆነና ዕረፍት የሌለበት
አንገት ያለሃሳብ የሚመዘዝበት
ልብ ከግንባር ላይ የሚነበብበት
ለጋነት ባጠራው ይሉኝታ ቢስ ፊትዋ
በስልት ያልተገራው ግልጽ አስተያየትዋ
መልሶ ቢያሳየው የራሱን አንካሳ
የባህሉን ጅራፍ የወጉን ጠባሳ
“ምነው ዓይን በላች ይሉኝታ አጣችሳ”“
እያለ ጮኸና ልቧን አስበርግጐ
ወሰደው ከፊትዋ ልጅነትዋን ጠርጐ
በሞረድ ምላሱ ፈግፍጐ ፈግፍጐ . . .
(ታገል ሠይፉ፣ ቀፎውን አትንኩት፣ 1986)
No comments:
Post a Comment