ሟሙቷል
አለልኝ መሀመድ
ሰሞኑን ነዉ፡፡ ከስራ ወጥቼ ቤቴ ስደርስ፤ ድብርብር አለኝ፡፡ ለምን እንደሆነ አልገባኝም፡፡ የምወዳት ልጅ
ቀጥራኝ ስለቀረች ግን አይደለም፡፡ በእርግጥ ሰዉ ቀጥሮኝ ሲቀር ይደብረኛል፡፡ ነገር ግን ቀጥራኝ የምትቀር አይነት
ሴት አላፈቅርም… ሲጀመር፡፡ ስለዚህ የድብረቴ ምክንያት ሌላ ነዉ፡፡፡
ለማንኛዉም፤ ከድብርት ለመላቀቅ ቤቴን ጥየ ወጣሁ፡፡ ከቤቴ ብዙም ሳይርቅ ደግሞ አንድት አነስ ያለች፤ ጫጫታ የማይበዛባት ካፌ አለች፡፡ የሄድኩት ወደ እዚች ካፌ ነበር፡፡ ስገባ ታድያ በሩ አካባቢ፤ በግምት፤ እዚች ምድር ላይ ለ47 አመታት ያህል የተሰቃየ የሚመስል አንድ ጎልማሳ፤ የነተበ ነጭ ሸሚዝ በቡኒ ጃኬት ለብሶ፤ በትልቅ ብርጭቆ የቀረበለትን ሻይ፤ በትንሽ ማንኪያ ያማስላል፡፡
ከሰዉየዉ ብዙም ሳልርቅ ፊት ለፊቱ ያለዉ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡፡ የካፌዋ አስተናጋጆች መግባቴን አይተዉ እስከሚታዘዙኝ ድረስ፤ ሰዉየዉን ማየት ጀመርኩ፡፡
ሰዉየዉ ረጋ ብሎ ሻዩን እያማሰለ፤ አይኑን በመስታወቱ አሳልፎ ዉጭዉን አሻግሮ ያያል፡፡ እኔም የማያገባኝን የዚህን ሰዉየ ሁኔታ ተመስጨ በመከታተል ላይ እያለሁ፤ አንዲት ቀጫጫ አስተናጋጅ ወደኔ መጣች፡፡
“ምን ልታዘዝ?”
“ማኪያቶ!” … አልኳት፡፡
“ነጣ ያለ ይሁንልህ ወይስ ጠቆር ያለ?”
“ይቅርታ ሻይ ማለቴ ነዉ፡፡ ማኪያቶዉን ተይዉ፡፡” … አልኳት፡፡
እሽ… ስትለኝ…”እንደዉም ማኪያቶ ይሁንልኝ በቃ፡፡ ሻዩን ተይዉ፡፡” አልኳት፡፡
ወዲያዉ ደግሞ …”ግን ሻይ ይሻለኛል መሰለኝ …” ስላት ተናዳ ይመስለኛል፤ ፊቷ ኮስተር ማለት ሲጀምር “ይቅርታ ተመልሰሽ ትመጪ እናትይ” አልኳት፡፡ (‘አስቤ ልንገርሽ’ ነገር ነዉ ሁኔታየ፡፡)
ልጅቷ ስትሄድ፤ ከሻይ እና ከማኪያቶ አንዱን መምረጥ ለምን እንደከበደኝ ማሰብ ጀምርኩ፡፡ ሲገባኝ ታድያ፤ ለካ ነገሩ እንዲህ ነዉ… መጠጣት የፈለኩት ማኪያቶ ነዉ፡፡ መጠጣት የምችለዉ ግን ሻይ ነዉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ቀን ላይ፤ ከምሳ በኋላ አንድ ማኪያቶ መጠጣቴ ነዉ፡፡ በቀን ሁለት ማኪያቶ የሚያስጠጣ አቅም እንደሌለኝ፤ እንኳን እኔ ማንም ያዉቃል፡፡
እንደዉም አንድ ኢኮኖሚስት ጓደኛየ እንደዚህ አይነት ሁኔታ ‘በኢኮኖሚክስኛ’ ‹‹በጀት ኮንስትሬይንት›› ተብሎ እንደሚጠራ ነግሮኛል፡፡ ግን ምን ዋጋ አለዉ፡፡ ያማረኝን ማኪያቶ ካላስጠጣኝ ቃሉ ምን ይጠቅመኛል…??? ስለዚህ ኢኮኖሚስቶቻችን እባካችሁ ቃሉን እና ትርጉሙን ከምትነግሩን፤ መንስኤዉንና መፍትሄዉን ንገሩን፡፡
ለማነኛዉም ችግሩ ‹‹በጀት ኮንስትሬይንት›› መሆኑ ሲገባኝ ልጅቷን ጠርቼ ያለምንም ማቅማማት ሻየን አዘዝኩኝና ሀሳቤን ሻይ ወደ ሚያማስለዉ ሰዉየ መለስኩት፡፡ ሰዉየዉ አሁንም ሻዩን ያማስላል፡፡ ሻዩን ግን አያየዉም፡፡
ያዘዝኩት ሻይ መጣና አይኔን ከሰዉየዉ ላይ ሳልነቅል ሻየን አማስየ ጠጣሁ፡፡ ሰዉየዉ ግን አሁንም ያማስላል፡፡ ሁኔታዉ ግራ ስለገባኝ አንገቴን አርዝሜ ሻዩ ዉስጥ ያለዉን ነገር ለማየት ሞከርኩ፡፡ ምንም የለም፡፡ ስኳሩም ሟሙቷል፡፡
እናም አላስችልህ ስላለኝ… ሰዉየዉን በእጄ ጠርቸ… “ይቅርታ ወንድም ሟሙቶልሀል፡፡” አልኩት፡፡ “ምኑ?” አለኝ፡፡ “ስኳሩ” አልኩት፡፡ “የምን ስኳር?…” ሲለኝ…”ማለት… ሻይ እያማሰልክ አይደል? ስኳሩ ማሙቷል ነዉ የምልህ፡፡ እንዳይቀዘቅዝብህ ብየ ነዉ::”… አልኩት ሻዩን በእጄ እየጠቆምኩ፡፡ ሰዉየዉም… “እ…እ…እ .. እሺ” አለና በሁኔታዉ እንደማፈር ብሎ ሻዩን ለመጀመሪያ ጊዜ ጐንበስ ብሎ አየዉ፡፡
እኔም፤ ባልጠበኩት ሁኔታ ሰዉየዉ ሲሸማቀቅ ሳየዉ፤ እራሴን ወቀስኩት፡፡ እናም.. “እስቲ እንደዚህ ከማሳቅቀዉ፤ መናለ ዝም ባልኩት ኖሮ…? ለዛዉም ለቀዘቀዘ ሻይ … ወይ መጀመሪያ አልነገረኩት… ምን አይነት ሰዉ ነኝ?…” እያልኩ ከራሴ ጋር እየተሟገትኩ ከካፌዉ ተነስቼ ወጣሁ፡፡ ሰዉየዉንና የሰዉየዉን ሻይ በሀሳቤ ይዤ ትንሽ እንደተራመድኩኝ ግን… “ወንድም … ወንድም…” የሚል ድምፅ ተሰማኝ፡፡ ዞር ስል የካፌዉ አስተናጋጅ ነች፡፡
“ይቅርታ ሂሳብ…” አለችኝ ፡፡
“የምን ሂሳብ” አልኳት፡፡
“የሻይ ሂሳብ፡፡” ስትለኝ
“የማን ሻይ?” አልኳት፡፡
እርሷም… “ማለት ሻይ ጠጥተህ የለ? ሂሳብ አልሰጠኸኝም…” ስትለኝ …የጠጣሁት ሻይ ትዝ አለኝና “እ…እ…እ… እሺ፡፡ ስንት ነዉ?” ስላት…”አምስት ብር ከ ሰባ ሳንቲም አለችኝ”. . . ዘና ብላ፡፡ (እኔ እርሷን ብሆን ሂሳቡን ለመናገር እሳቀቅ ነበር::)
እናም፤ ብሩን ከፍየ፤ ድብርቴም ከበፊቱ ብሶ ወደ ቤቴ ተመለስኩ እላችኋለሁ፡፡ ግን ጭንቅላቴ ዉስጥ ሲመላለስ የነበረዉን አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ምናልባት የናንተም ጥያቄ ከሆነ፡፡
****
እኔን፤ ማኪያቶ መጠጣት እየፈለኩ፤ ሻይ ያስጠጣኝ…፤ ሰዉየዉን ከ አምስት ደቂቃ በላይ ሻይ እንዲያማስል ያደረገዉ…፤ በስተመጨረሻም እኔና ሰዉየዉ እንድንሸማቀቅ ያደረገን…፤ እንዲሁም አስተናጋጇን ሂሳብ ለመቀበል ዉጭ ድረስ እንድትሄድ ያደረጋት…ምክንያቱ ምን ይሆን?
የኑሮ ዉድነቱ ይሆን?
ለማንኛዉም፤ ከድብርት ለመላቀቅ ቤቴን ጥየ ወጣሁ፡፡ ከቤቴ ብዙም ሳይርቅ ደግሞ አንድት አነስ ያለች፤ ጫጫታ የማይበዛባት ካፌ አለች፡፡ የሄድኩት ወደ እዚች ካፌ ነበር፡፡ ስገባ ታድያ በሩ አካባቢ፤ በግምት፤ እዚች ምድር ላይ ለ47 አመታት ያህል የተሰቃየ የሚመስል አንድ ጎልማሳ፤ የነተበ ነጭ ሸሚዝ በቡኒ ጃኬት ለብሶ፤ በትልቅ ብርጭቆ የቀረበለትን ሻይ፤ በትንሽ ማንኪያ ያማስላል፡፡
ከሰዉየዉ ብዙም ሳልርቅ ፊት ለፊቱ ያለዉ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡፡ የካፌዋ አስተናጋጆች መግባቴን አይተዉ እስከሚታዘዙኝ ድረስ፤ ሰዉየዉን ማየት ጀመርኩ፡፡
ሰዉየዉ ረጋ ብሎ ሻዩን እያማሰለ፤ አይኑን በመስታወቱ አሳልፎ ዉጭዉን አሻግሮ ያያል፡፡ እኔም የማያገባኝን የዚህን ሰዉየ ሁኔታ ተመስጨ በመከታተል ላይ እያለሁ፤ አንዲት ቀጫጫ አስተናጋጅ ወደኔ መጣች፡፡
“ምን ልታዘዝ?”
“ማኪያቶ!” … አልኳት፡፡
“ነጣ ያለ ይሁንልህ ወይስ ጠቆር ያለ?”
“ይቅርታ ሻይ ማለቴ ነዉ፡፡ ማኪያቶዉን ተይዉ፡፡” … አልኳት፡፡
እሽ… ስትለኝ…”እንደዉም ማኪያቶ ይሁንልኝ በቃ፡፡ ሻዩን ተይዉ፡፡” አልኳት፡፡
ወዲያዉ ደግሞ …”ግን ሻይ ይሻለኛል መሰለኝ …” ስላት ተናዳ ይመስለኛል፤ ፊቷ ኮስተር ማለት ሲጀምር “ይቅርታ ተመልሰሽ ትመጪ እናትይ” አልኳት፡፡ (‘አስቤ ልንገርሽ’ ነገር ነዉ ሁኔታየ፡፡)
ልጅቷ ስትሄድ፤ ከሻይ እና ከማኪያቶ አንዱን መምረጥ ለምን እንደከበደኝ ማሰብ ጀምርኩ፡፡ ሲገባኝ ታድያ፤ ለካ ነገሩ እንዲህ ነዉ… መጠጣት የፈለኩት ማኪያቶ ነዉ፡፡ መጠጣት የምችለዉ ግን ሻይ ነዉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ቀን ላይ፤ ከምሳ በኋላ አንድ ማኪያቶ መጠጣቴ ነዉ፡፡ በቀን ሁለት ማኪያቶ የሚያስጠጣ አቅም እንደሌለኝ፤ እንኳን እኔ ማንም ያዉቃል፡፡
እንደዉም አንድ ኢኮኖሚስት ጓደኛየ እንደዚህ አይነት ሁኔታ ‘በኢኮኖሚክስኛ’ ‹‹በጀት ኮንስትሬይንት›› ተብሎ እንደሚጠራ ነግሮኛል፡፡ ግን ምን ዋጋ አለዉ፡፡ ያማረኝን ማኪያቶ ካላስጠጣኝ ቃሉ ምን ይጠቅመኛል…??? ስለዚህ ኢኮኖሚስቶቻችን እባካችሁ ቃሉን እና ትርጉሙን ከምትነግሩን፤ መንስኤዉንና መፍትሄዉን ንገሩን፡፡
ለማነኛዉም ችግሩ ‹‹በጀት ኮንስትሬይንት›› መሆኑ ሲገባኝ ልጅቷን ጠርቼ ያለምንም ማቅማማት ሻየን አዘዝኩኝና ሀሳቤን ሻይ ወደ ሚያማስለዉ ሰዉየ መለስኩት፡፡ ሰዉየዉ አሁንም ሻዩን ያማስላል፡፡ ሻዩን ግን አያየዉም፡፡
ያዘዝኩት ሻይ መጣና አይኔን ከሰዉየዉ ላይ ሳልነቅል ሻየን አማስየ ጠጣሁ፡፡ ሰዉየዉ ግን አሁንም ያማስላል፡፡ ሁኔታዉ ግራ ስለገባኝ አንገቴን አርዝሜ ሻዩ ዉስጥ ያለዉን ነገር ለማየት ሞከርኩ፡፡ ምንም የለም፡፡ ስኳሩም ሟሙቷል፡፡
እናም አላስችልህ ስላለኝ… ሰዉየዉን በእጄ ጠርቸ… “ይቅርታ ወንድም ሟሙቶልሀል፡፡” አልኩት፡፡ “ምኑ?” አለኝ፡፡ “ስኳሩ” አልኩት፡፡ “የምን ስኳር?…” ሲለኝ…”ማለት… ሻይ እያማሰልክ አይደል? ስኳሩ ማሙቷል ነዉ የምልህ፡፡ እንዳይቀዘቅዝብህ ብየ ነዉ::”… አልኩት ሻዩን በእጄ እየጠቆምኩ፡፡ ሰዉየዉም… “እ…እ…እ .. እሺ” አለና በሁኔታዉ እንደማፈር ብሎ ሻዩን ለመጀመሪያ ጊዜ ጐንበስ ብሎ አየዉ፡፡
እኔም፤ ባልጠበኩት ሁኔታ ሰዉየዉ ሲሸማቀቅ ሳየዉ፤ እራሴን ወቀስኩት፡፡ እናም.. “እስቲ እንደዚህ ከማሳቅቀዉ፤ መናለ ዝም ባልኩት ኖሮ…? ለዛዉም ለቀዘቀዘ ሻይ … ወይ መጀመሪያ አልነገረኩት… ምን አይነት ሰዉ ነኝ?…” እያልኩ ከራሴ ጋር እየተሟገትኩ ከካፌዉ ተነስቼ ወጣሁ፡፡ ሰዉየዉንና የሰዉየዉን ሻይ በሀሳቤ ይዤ ትንሽ እንደተራመድኩኝ ግን… “ወንድም … ወንድም…” የሚል ድምፅ ተሰማኝ፡፡ ዞር ስል የካፌዉ አስተናጋጅ ነች፡፡
“ይቅርታ ሂሳብ…” አለችኝ ፡፡
“የምን ሂሳብ” አልኳት፡፡
“የሻይ ሂሳብ፡፡” ስትለኝ
“የማን ሻይ?” አልኳት፡፡
እርሷም… “ማለት ሻይ ጠጥተህ የለ? ሂሳብ አልሰጠኸኝም…” ስትለኝ …የጠጣሁት ሻይ ትዝ አለኝና “እ…እ…እ… እሺ፡፡ ስንት ነዉ?” ስላት…”አምስት ብር ከ ሰባ ሳንቲም አለችኝ”. . . ዘና ብላ፡፡ (እኔ እርሷን ብሆን ሂሳቡን ለመናገር እሳቀቅ ነበር::)
እናም፤ ብሩን ከፍየ፤ ድብርቴም ከበፊቱ ብሶ ወደ ቤቴ ተመለስኩ እላችኋለሁ፡፡ ግን ጭንቅላቴ ዉስጥ ሲመላለስ የነበረዉን አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ምናልባት የናንተም ጥያቄ ከሆነ፡፡
****
እኔን፤ ማኪያቶ መጠጣት እየፈለኩ፤ ሻይ ያስጠጣኝ…፤ ሰዉየዉን ከ አምስት ደቂቃ በላይ ሻይ እንዲያማስል ያደረገዉ…፤ በስተመጨረሻም እኔና ሰዉየዉ እንድንሸማቀቅ ያደረገን…፤ እንዲሁም አስተናጋጇን ሂሳብ ለመቀበል ዉጭ ድረስ እንድትሄድ ያደረጋት…ምክንያቱ ምን ይሆን?
የኑሮ ዉድነቱ ይሆን?
No comments:
Post a Comment