Jan 2, 2014

ሟሙቷል:

ሟሙቷል

 አለልኝ መሀመድ ሰሞኑን ነዉ፡፡ ከስራ ወጥቼ ቤቴ ስደርስ፤ ድብርብር አለኝ፡፡ ለምን እንደሆነ አልገባኝም፡፡ የምወዳት ልጅ ቀጥራኝ ስለቀረች ግን አይደለም፡፡ በእርግጥ ሰዉ ቀጥሮኝ ሲቀር ይደብረኛል፡፡ ነገር ግን ቀጥራኝ የምትቀር አይነት ሴት አላፈቅርም… ሲጀመር፡፡ ስለዚህ የድብረቴ ምክንያት ሌላ ነዉ፡፡፡
ለማንኛዉም፤ ከድብርት ለመላቀቅ ቤቴን ጥየ ወጣሁ፡፡ ከቤቴ ብዙም ሳይርቅ ደግሞ አንድት አነስ ያለች፤ ጫጫታ የማይበዛባት ካፌ አለች፡፡ የሄድኩት ወደ እዚች ካፌ ነበር፡፡ ስገባ ታድያ በሩ አካባቢ፤ በግምት፤ እዚች ምድር ላይ ለ47 አመታት ያህል የተሰቃየ የሚመስል አንድ ጎልማሳ፤ የነተበ ነጭ ሸሚዝ በቡኒ ጃኬት ለብሶ፤ በትልቅ ብርጭቆ የቀረበለትን ሻይ፤ በትንሽ ማንኪያ ያማስላል፡፡
ከሰዉየዉ ብዙም ሳልርቅ ፊት ለፊቱ ያለዉ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ፡፡ የካፌዋ አስተናጋጆች መግባቴን አይተዉ እስከሚታዘዙኝ ድረስ፤ ሰዉየዉን ማየት ጀመርኩ፡፡
ሰዉየዉ ረጋ ብሎ ሻዩን እያማሰለ፤ አይኑን በመስታወቱ አሳልፎ ዉጭዉን አሻግሮ ያያል፡፡ እኔም የማያገባኝን የዚህን ሰዉየ ሁኔታ ተመስጨ በመከታተል ላይ እያለሁ፤ አንዲት ቀጫጫ አስተናጋጅ ወደኔ መጣች፡፡
“ምን ልታዘዝ?”
“ማኪያቶ!” … አልኳት፡፡
“ነጣ ያለ ይሁንልህ ወይስ ጠቆር ያለ?”
“ይቅርታ ሻይ ማለቴ ነዉ፡፡ ማኪያቶዉን ተይዉ፡፡” … አልኳት፡፡
እሽ… ስትለኝ…”እንደዉም ማኪያቶ ይሁንልኝ በቃ፡፡ ሻዩን ተይዉ፡፡” አልኳት፡፡
ወዲያዉ ደግሞ …”ግን ሻይ ይሻለኛል መሰለኝ …” ስላት ተናዳ ይመስለኛል፤ ፊቷ ኮስተር ማለት ሲጀምር “ይቅርታ ተመልሰሽ ትመጪ እናትይ” አልኳት፡፡ (‘አስቤ ልንገርሽ’ ነገር ነዉ ሁኔታየ፡፡)
ልጅቷ ስትሄድ፤ ከሻይ እና ከማኪያቶ አንዱን መምረጥ ለምን እንደከበደኝ ማሰብ ጀምርኩ፡፡ ሲገባኝ ታድያ፤ ለካ ነገሩ እንዲህ ነዉ… መጠጣት የፈለኩት ማኪያቶ ነዉ፡፡ መጠጣት የምችለዉ ግን ሻይ ነዉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ቀን ላይ፤ ከምሳ በኋላ አንድ ማኪያቶ መጠጣቴ ነዉ፡፡ በቀን ሁለት ማኪያቶ የሚያስጠጣ አቅም እንደሌለኝ፤ እንኳን እኔ ማንም ያዉቃል፡፡
እንደዉም አንድ ኢኮኖሚስት ጓደኛየ እንደዚህ አይነት ሁኔታ ‘በኢኮኖሚክስኛ’ ‹‹በጀት ኮንስትሬይንት›› ተብሎ እንደሚጠራ ነግሮኛል፡፡ ግን ምን ዋጋ አለዉ፡፡ ያማረኝን ማኪያቶ ካላስጠጣኝ ቃሉ ምን ይጠቅመኛል…??? ስለዚህ ኢኮኖሚስቶቻችን እባካችሁ ቃሉን እና ትርጉሙን ከምትነግሩን፤ መንስኤዉንና መፍትሄዉን ንገሩን፡፡
ለማነኛዉም ችግሩ ‹‹በጀት ኮንስትሬይንት›› መሆኑ ሲገባኝ ልጅቷን ጠርቼ ያለምንም ማቅማማት ሻየን አዘዝኩኝና ሀሳቤን ሻይ ወደ ሚያማስለዉ ሰዉየ መለስኩት፡፡ ሰዉየዉ አሁንም ሻዩን ያማስላል፡፡ ሻዩን ግን አያየዉም፡፡
ያዘዝኩት ሻይ መጣና አይኔን ከሰዉየዉ ላይ ሳልነቅል ሻየን አማስየ ጠጣሁ፡፡ ሰዉየዉ ግን አሁንም ያማስላል፡፡ ሁኔታዉ ግራ ስለገባኝ አንገቴን አርዝሜ ሻዩ ዉስጥ ያለዉን ነገር ለማየት ሞከርኩ፡፡ ምንም የለም፡፡ ስኳሩም ሟሙቷል፡፡
እናም አላስችልህ ስላለኝ… ሰዉየዉን በእጄ ጠርቸ… “ይቅርታ ወንድም ሟሙቶልሀል፡፡” አልኩት፡፡ “ምኑ?” አለኝ፡፡ “ስኳሩ” አልኩት፡፡ “የምን ስኳር?…” ሲለኝ…”ማለት… ሻይ እያማሰልክ አይደል? ስኳሩ ማሙቷል ነዉ የምልህ፡፡ እንዳይቀዘቅዝብህ ብየ ነዉ::”… አልኩት ሻዩን በእጄ እየጠቆምኩ፡፡ ሰዉየዉም… “እ…እ…እ .. እሺ” አለና በሁኔታዉ እንደማፈር ብሎ ሻዩን ለመጀመሪያ ጊዜ ጐንበስ ብሎ አየዉ፡፡
እኔም፤ ባልጠበኩት ሁኔታ ሰዉየዉ ሲሸማቀቅ ሳየዉ፤ እራሴን ወቀስኩት፡፡ እናም.. “እስቲ እንደዚህ ከማሳቅቀዉ፤ መናለ ዝም ባልኩት ኖሮ…? ለዛዉም ለቀዘቀዘ ሻይ … ወይ መጀመሪያ አልነገረኩት… ምን አይነት ሰዉ ነኝ?…” እያልኩ ከራሴ ጋር እየተሟገትኩ ከካፌዉ ተነስቼ ወጣሁ፡፡ ሰዉየዉንና የሰዉየዉን ሻይ በሀሳቤ ይዤ ትንሽ እንደተራመድኩኝ ግን… “ወንድም … ወንድም…” የሚል ድምፅ ተሰማኝ፡፡ ዞር ስል የካፌዉ አስተናጋጅ ነች፡፡
“ይቅርታ ሂሳብ…” አለችኝ ፡፡
“የምን ሂሳብ” አልኳት፡፡
“የሻይ ሂሳብ፡፡” ስትለኝ
“የማን ሻይ?” አልኳት፡፡
እርሷም… “ማለት ሻይ ጠጥተህ የለ? ሂሳብ አልሰጠኸኝም…” ስትለኝ …የጠጣሁት ሻይ ትዝ አለኝና “እ…እ…እ… እሺ፡፡ ስንት ነዉ?” ስላት…”አምስት ብር ከ ሰባ ሳንቲም አለችኝ”. . . ዘና ብላ፡፡ (እኔ እርሷን ብሆን ሂሳቡን ለመናገር እሳቀቅ ነበር::)
እናም፤ ብሩን ከፍየ፤ ድብርቴም ከበፊቱ ብሶ ወደ ቤቴ ተመለስኩ እላችኋለሁ፡፡ ግን ጭንቅላቴ ዉስጥ ሲመላለስ የነበረዉን አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ምናልባት የናንተም ጥያቄ ከሆነ፡፡
****
እኔን፤ ማኪያቶ መጠጣት እየፈለኩ፤ ሻይ ያስጠጣኝ…፤ ሰዉየዉን ከ አምስት ደቂቃ በላይ ሻይ እንዲያማስል ያደረገዉ…፤ በስተመጨረሻም እኔና ሰዉየዉ እንድንሸማቀቅ ያደረገን…፤ እንዲሁም አስተናጋጇን ሂሳብ ለመቀበል ዉጭ ድረስ እንድትሄድ ያደረጋት…ምክንያቱ ምን ይሆን?
የኑሮ ዉድነቱ ይሆን?

Oct 29, 2013

ሠላይና ተሠላይ፤ ወዳጅና ጠላት

አሜሪካዊ እንደራሴና የሥለላ ጉዳይ አዋቂ ፔተ ሆክስትራን የሚያስደንቀዉ ግን የአሜሪካ ሰላዮች የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥትን ስልክን መጥለፋቸዉ አይደለም።የነፍሬድሪሽ ቁጣና ብስጭት እንጂ።ሆክስትራ እንደሚሉት ካስደነቀ-የሚያስደንቀዉ የጀርመን መሪ ሥልክ መጠለፉን ፍሬድሪሽ የሚመሩት የጀርመን የስለላ ድርጅት አለማወቁ ነዉ።
ARCHIV - US-Präsident Barack Obama und Bundeskanzlerin Angela Merkel unterhalten sich am 18.06.2012 in Los Cabos, Mexiko, beim Familienfoto. Merkel setzt bei der Aufklärung der millionenfachen Datensammlung des Geheimdienstes NSA nun auf eine Reise von Vertretern der Bundesregierung und deutscher Geheimdienste in der nächsten Woche nach Washington. Foto: Peer Grimm dpa (zu dpa Merkel verspricht größtmögliche Offenheit bei US-Ausspähaffäre vom 05.07.2013) +++(c) dpa - Bildfunk+++ ወዳጁ ናቸዉ
ለካሳትሮ፥ ለብሬዥነቭ፥ ለማኦ፥ ለ ደጎል፥ ለንጎ በርግጥ አዲስ አልነበረም።አይደለምም።የኤንርኮ ፔና ኔቶ ኢሜል መጠለፍ- ጉድ አሰኝቶ ነበር።የዲልማ ሮሴፍ-ኢሜል መጠለፍ-አስደንቆ ነበር።የሜርክል ሥልክ መጠለፍስ? ጉዱን ጉድ ዘለቀዉ-እንበል ይሆን።የስላላዉ ቅሌት መነሻ፥ዳራዉ ማጣቃሻ፥ የፖለቲካዉ እድምታዉ መድረሻችን ነዉ-ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።


ሚዚያ ሃያ-አንድ 1943 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ።) ፈረንሳይን ከናዚ ጀርመኖች አገዛዝ ነፃ ለማዉጣት የሚዋጋዉ ጦር አዛዥ ጄኔራል ሻርል ደጎል የነፃዋ ፈረንሳይ ባሕር ሐይል ጦርን ለመጎብኘት ከተጠጉባት ብሪታንያ በብሪታንያ አዉሮፕላን ተሳፈሩ።ቆፍጣናዉ፥ ቁጡዉ፥ እልሐኛዉ ረጅሙ ጄኔራል ከትንሿ አዉሮፕላን እንደተሳፈሩ አብራሪዉ (ፓይለቱ) አዉሮፕላንኗን እንደማስነሳት ትንሽ አንገጫገጨና ወዲዚያዉ አቆማት።ጉዞዉ ተዘረዘ።

አዉሮፕላንኗ ስትፈተሽ የሞተሯ አካል በአሲድ መበላሸቱ ታወቀ።አሲዱን አዉሮፕላንዋ አካል ላይ የረጨዉ ወገን ማንነት-እስካሁን ሚስጥር ነዉ።ጄኔራሉ ግን ያኔዉኑ «የብሪታንያ ሰላዮች ሻጥር» ለማለት አላመነቱም።የአዉሮጳ እብሪተኞች የለኮሱት ጦርነት ዓለምን በሚያነድበት በዚያ ዘመን ወዳጅን ከጠላት መለየቱ-ከባድ ነበር።በዚሕም ሰበብ ደ ጎል እንደጠረጠሩት ብሪታንያዎች አድርገዉት ከነበር-ብዙዎችን ብዙም አላስደነቀም ነበር።
ARCHIV - US-Präsident Barack Obama (r) wischt sich am 19.06.2013 den Schweiß von der Stirn neben Kanzlerin Angela Merkel auf einem Podium vor dem Brandenburger Tor am Pariser Platz in Berlin. Foto: Marcus Brandt/dpa (zu dpa Obama war angeblich in NSA-Abhörattacken gegen Merkel eingeweiht vom 27.10.2013) +++(c) dpa - Bildfunk+++ ተሠላይና አሰላይ


ከብዙ አመታት በሕዋላ የደጎልን ቤተ-መንግሥት የተረኩቡት ፕሬዝዳት ኒኮላ ሳርኮዚ ከጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት ከወይዘሮ አንጌላ ሜርክል ጋር የነበራቸዉ ግንኙነት ከመሪዎች-ወዳጅነትም ጠንከር፥ ጠለቅ ያለ-ነበር ይባላል።ሳርኮዚ ከሜርክል ጋር ሥላላቸዉ ግንኙነት ሥለሚያደርጉት ዉይይት ሲጠየቁ፥«ሁሌ እንገናኛለን፥ በስልክ፥ እንነጋገር፥ ኤስ ኤም ኤስ እንለዋወጣለንም» እያሉ የግንኙነት ዉይይታቸዉ ደረጃ ዘርዝረዉ ነበር።

የሜርክል መልዕክት ከሳርኮዚ አይን-ጆሮ በሚደርስበት ፍጥነት ከአሜሪካ ሰላዮች ኮምፒዉተር ላይ ይዘረገፍ ነበር።ይሕን በርግጥ ሳርኮዚም፥ ሜርክልም ከኛ እኩል ያወቁት ሰሞኑን ነዉ።NSA በሚል ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ የአሜሪካ ብሔራዊ የሥለላ ድርጅት ባልደረባ የነበሩት ቶማስ ድራክ እንደሚሉት ሜርክልን መሠለል ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲን መጣስ ነዉ።

«ይሕ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲን ክፉኛ መጣስ ነዉ።ይሕ ለመራሒተ-መንግሥት ሜርክል የግል ጉዳይ ነዉ።የግላቸዉ ተንቀሳቃሽ ሥልክ ነዉ።(ያን መጥለፍ) ለምን አስፈለገ።ከእዉነኛ ጠላትሕ ጋር በምታደርገዉ ዉጊያ የቅርብ ተባባሪሕን?»


ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ፥ ዓለም አቀፍ ሕግ በቀዝቃዛዉ ጦርነት ወቅት ነበር።ዛሬም አለ።አንዴም ግን ተከብሮ አያዉቅም።ሕግ፥ ደንብ፥ ሥምምነቱን የሚጥሰዉ ደግሞ ሕግ-ደንቡን ካወጣዉ፥ አስከብረዋለሁ ከሚለዉ ሐያል ዓለም ሌላ ማንም አይደለም።

በቀዝቃዉ ጦርነት ወቅት ልክ እንደ ዓለም አቀፉ ሕግ ደንብ ሁሉ የሞስኮ፥ ቤጂንግ ተባባሪዎች፥ የለንደን-ዋሽግተን፥የቦን ፓሪስ ተሻራኪዎች ጎራ ለይተዉ አንዱ የሌላዉን ሚስጥር ማጭለጉ የፖለቲካዉ ፈሊጥ፥ የስለላዉ ወግ ነበር።

የሐገር መሪዎችን እንቅስቃሴ መከታተል አይደለም መግደል ማስገደልም የፖለቲካ መርሕን የማጠናከር፥ ርዕዮተ-ዓለምን የማዳን-ማስፋፋት ሥልት አካል ነበር።የአሜሪካዉ ማዕከላዊ የሥለላ ድርጅት CIA ሹም ኮሎኔል ጄ ሲ ኪንግ የኩባዉን ኮሚንስታዊ መሪ ፊደል ካስትሮ-ከማስገደል ሌላ ሌላ አመራጭ እንደለሌ የጠቆሙት በ1959 ነበር።

ያኔ ዓለም አቀፍ ማሕበር ዲፕሎማሲ፥ ሕግም ነበር።ዲፕሎማሲ ሕግ፥ ደንቡ የሚረቀቅ፥ የሚወሰን የሚበየነዉ ደግሞ ከኒዮርክ ነበር፥ ከዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ።የአሜሪካዊ ማዕከላዊ የሥለላ ድርጅት CIA ካስትሮን ለማስገደል ስድስት መቶ ሰላሳ-ስምንት ጊዜ ያደረገዉ ወይም አድርጓል የተባለዉ ሙከራ የብዙ መፅሐፍት፥ የዝነኛ ፊልም ርዕሥም ሆኗል።

አያቱላሆች የቴሕራንን ቤተ-መንግሥት ከተቆጣጠሩበት ከ1979 ጀምሮ ኢራን የእስራኤልም፥ የአሜሪካኖችም አሜሪካኖችን የሚመሩት የምዕራቡ ዓለምም ቀንደኛ ጠላት ናት።በሕዝብ የተመረጡት የኢራን ጠቅላይ ሚንስትር መሐመድ ሞስዳቅሕን በ1953 ከስልጣን ያስወገደዉ ማን ነበር? ፓትሪስ ሉምባ እንዴት-እና ማን ገደላቸዉ።ራፋኤል ሊኒዳስ ትሩሔሎስ፥ ንጎ ዲንሕ ዲየምንስ?
US-Bürger demonstrieren am 24.10.2013 nahe dem Kapitol in Washington DC gegen die Überwachung durch Geheimdienste wie die NSA. (Foto: Monika Griebeler / DW) - eingestellt von Andreas Grigo ተቃዉሞ


ጥያቄዉ-ጥያቄ ይወልዳል እንጂ ማብቂያ የለዉም።ዓለምን የሚመራዉ ግን ዓለም አቀፉ ሕግ ዲፕሎማሲ ሳይሆን የሐያላን ፍላጎትና ፍቃድ መሆኑ ሐቅ ነዉ።የሐያላኑን ፍላጎት ለማስከበር ደግሞ በግልፅ የሚታወቀዉ ሐያላኑ ወዳጅ ከሚሉት ጋር መተባበር መሻረክ መወዳጀታቸዉ ነበር።እስከ 2007 ድረስ በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የስለላ ጉዳይ ኮሚቴ ሊቀመንበር የነበሩት ፔተ ሆክስትራ እንደሚሉት ግን በስለላዉ ዓለም ከወዳጅም-መሐል ተጠርጣሪ ወዳጅ አለ።

«ይሕ ሊሆን የሚችል ይመስለኛል።በስለላዉ ዓለም ፈረንሳዮች፥ ጀርመኖች፥ እስራኤሎች አሜሪካኖች ሁላችንም ጥሩ ወዳጆች ነን።ግን አንዳችን ሌላችንን የምንሠልልበት ጊዜ ሊኖርም ይችላል-የሚል መግባባት ያለ ይመስለኛል።ይሕ (በሰላዮች ዘንድ) በጣም በጣም የታወቀ ነዉ።»

ኮሚንስቶች የሐቫና፥ የሳንዲያጎ፥ የማናጉዋ የሌሎችንም የደቡብ አሜሪካ ሐገራት አብያተ-መንግሥታትን ሲቆጣጠሩ ወይም ለመቆጣጠር ሲያሰጉ የዩናይትድ ስቴትስዋ የቅርብ ጎረቤት፥ ታማኝ፥ ታዛዥነቷን አጓድላ አታዉቅም።ሜክሲኮ።

ከቀዝቃዛዉ ጦርነት በሕዋላ እነ-ሑጎ ሻቬዝ አሜሪካኖችን የሚቃወም ግንባር ለመፍጠር ሲፍጨረጨሩም ያቺ-የአሜሪካ የቅርብ ጎረቤት በታማኝ ታዛዥነቷ እንደፀናች ነበር።ነዉም።ኤንሪክ ፔና ኒቶ ለፕሬዝዳትነት ሲወዳደሩ-ሲመረጡም እንደ ብዙ ቀዳሚዎቻቸዉ ሁሉ ለሐያል፥ ሐብታም፥ ታላቅ ጎረቤታቸዉ ታማኝ ታዥነታቸዉን እንደጠበቁ ነዉ።

በእጩነት ከተመዘገቡ ጀምሮ በምርጫዉ ካሸነፉ-ለሚንስትርነት የሚሾሙ የሚሽሩትን ፖለቲከኛ ስብዕና ማንነት፥ የሚዘረዝር፥ የምርጫ ዘመቻቸዉን ሥልት የሚያትት መልዕክት ለወዳጅ ተከታዮቻቸዉ ኢሜይል ይፅፋሉ። የNSA ሰላዮች ዋሽግተን ቁጭ ብለዉ የሜክሲኮዉን ፕሬዝዳት ኢሜይል ከፕሬዝዳንቱ ደጋፊ፥ተከታዮች እኩል ያነቡ ነበር።የብራዚሏ ፕሬዝዳት የወይዘሮ ዲልማ ሮሴፍ ኢሜዬልም-እንደዚያዉ ነዉ።

አሜሪካዊዉ ሠላይ ኤድዋርድ ስኖደን ሐገር መስሪያ ቤቱን ክዶ ከኮበለለ ወዲሕ የማይሰማ ጉድ የለም።አንዳድ ዘገቦች እንደሚጠቁሙት የሶቬት ሕብረት ኮሚንስቶች በስታሊን ዘመን የሶቬት ሕብረት ሕዝብ ከሚሠልሉት በላይ የአሜሪካ መንግሥት አሜሪካዉያንን ይሰልላል።ለአሜሪካ ሕዝብ ያልራራ ሥርዓት የፈረንሳይ ኩባንያዮችን፥ የስጳኝ ፖለቲከኞችን፥ የዓለምን ሕዝብ የሜክሲኮ፥ የብራዚል፥ የሌሎች ከሰላሳ በላይ መሪዎችን ቢሰልል-በርግጥ ሊያስደንቅ አይገባም።

ያምሆኖ የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት የሥልክ መልዕክት መጠለፉን ከአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት እስከ ሩሲያ መሪዎች ተቃዉመዋል።የጀርመን ፖለቲከኞች የሜርክል ደጋፊም ሆኑ ተቃዋሚዎችም እኩል አዉግዘዉታል።

«እንደሚመስለኝ ይሕ በጀርመን-አሜሪካኖችን ግንኙነት ያለዉን መተማመን ክፉኛ የሚጎዳ ነዉ።መተማመኑ ዳግም ሊገነባ የሚችለዉ እዉነታዉ በግልፅ ወጥቶ ማየን ከቻልን በኋላ ነዉ።

ይላሉ፥-የዋነኛዉ ተቃዋሚ ፓርቲ የSPD የምክር ቤት እንደራሴዎች አስተባባሪ ቶማስ ኦፐርማን ።ሥለ ጀርመን እና ጀርመንን የሚመለከቱ መረጃዎችን የመሰብሰብ መከታተሉ ሐላፊነት የጀርመን የሥለላ ድርጅት ነዉ።ቡንደስ ናሕሪሽተን ዲንስት።BND በጀርመንኛ ምሕፃሩ። የስለላዉን ድርጅት በበላይነት የሚያስተዳድርና የሚመራዉ ደግሞ የጀርመን ፌደራዊ የሐገር ዉስጥ ጉዳይ ሚንስቴር ነዉ።

የሐገር ዉስጥ ጉዳይ ሚንስትር ሐንስ ፔተር ፍሬድሪሽ ግን የመሪያቸዉን መሰለል እንደማንኛዉም ሰዉ ከመገናኛ ዘዴዎች የሰሙ ያክል ነዉ-የተቆጡት።

«ከአሜሪካኖች ጋር በዚሕ ሁኔታ አንሰራም።መተማመኑ ተበላሽቷል።እና እንደሚመስለኝ የተበላሸዉን መተማመን ለመጠገን ሁነኛ እርምጃ መወሰድ አለበት።»

አሜሪካዊ እንደራሴና የሥለላ ጉዳይ አዋቂ ፔተ ሆክስትራን የሚያስደንቀዉ ግን የአሜሪካ ሰላዮች የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥትን ስልክን መጥለፋቸዉ አይደለም።የነፍሬድሪሽ ቁጣና ብስጭት እንጂ።ሆክስትራ እንደሚሉት ካስደነቀ-የሚያስደንቀዉ የጀርመን መሪ ሥልክ መጠለፉን ፍሬድሪሽ የሚመሩት የጀርመን የስለላ ድርጅት አለማወቁ ነዉ።

«የዋሕነት ይመስለኛል።የጀርመን መንግሥት (ባለሥልጣናት) በወዳጆቻቸዉ ሊሰለሉ እንደሚችሉ ማወቅ ነበረባቸዉ።ነገሩ ከተፈፀመ አስደናቂዉ ነገር የሚመስለኝ፥ (ሥለላዉን) ለማስቆም የጀርመን የስለላ ማሕበረሰብ አስፈላጊዉ አፀፋ-እርምጃ አለመዉሰዱ ነዉ።»


Titel: Demonstration #stopwatchingus gegen NSA und Überwachung in Washington, DC, USA
Schlagworte: NSA, Überwachung, Demonstration, stopwatchingus
Wer hat das Bild gemacht?: Monika Griebeler
Wann wurde das Bild gemacht?: 26.10.2013
Wo wurde das Bild aufgenommen?: Washington, DC, USA ተቃዉሞ
የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት ስልክ መጠለፉ-መሰላላቸዉም እርግጥ ነዉ።ሜርክል መሰለላቸዉን ፕሬዝዳት ባራክ ኦቦማ ያዉቃሉ-አያዉቁም እያነጋገረ ነዉ።ካወቁ ከመቼ ጀምሮ የሚለዉም ያጠያይቃል። እራሳቸዉ ሜርክል እና የፈረንሳዩ ፕሬዝዳት ፍራንሷ ኦሎንድ የአዉሮጳ ሕብረት ወክለዉ ለኦባማ አቤቱታ ያቀርባሉ። ወደ አንድ ሺሕ የተገመቱ አሜሪካኖች በመንግሥታቸዉ መሠለላቸዉን በአደባባይ ሠልፍ አዉግዘዋል።አቤቱታ፥ ተቃዉሞ፥ ዉግዘት፥ ሰልፉ ምናልባት ይቀጥል ይሆናል፥ መሳለል-መጠላለፉ ያስቆመዋል ባይ ግን የለም።ምክንያት፥-ድሮ እንዲያ ነበር፥ ዛሬ እንዲያ ነዉ።ነገም።በዚሕ ዝግጅት ላይ ያላችሁን አስተያየት ላኩል። ማሕደረ ዜና ቢቃኘዉ ጥሩ ነዉ ብላችሁ የምትገምቱትን ወቅታዊ፥ ብሔራዊ፥ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ በተለመደዉ አድራሻችን ጠቁሙን።ለዛሬዉ ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰመን።

Oct 27, 2013

ኢትዬጲያ ቡና ከ ቲፒ ማዚምቤ በአዲስ አበባ…—600 ታዋቂ ሰዎች ይመጣሉ!


ሞ ኢብራሂም የተባለዉ ልጥጥ ሀብታም በየአመቱ የአፍሪካ ጥሩ ሰሪ መሪዎችን በመሸለም ይታወቃል፤ሞ ፋዉንዴሽን የተባለዉ የእርዳታ ድርጅቱ ከዚህ በፊት እንደ ማንዴላ እና መሰል መሪዎችን በመሸለም ይታወቃል፤ለምሳሌ አንዴ የአመቱ ምርጥ የአፍሪካ መሪ ተብሎ የተመረጠ ሰዉ 5ሚልየን ዶላር ብር ስጦታ ከዛም በየአመቱ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ 200ሺ ዶላር ይበረክትለታል፤ዘንድሮ ከ48ት የአፍሪካ ሀገራት ለዚህ የሚመጥን ሰዉ አልተገኘም፤ነገር ግን ፕሮግራሙ ያለ ተመራጭ መሪ በሙዚቃ ሰዎች በእግር ኳስ ዉድድር ይካሄዳል፤600 ታዋቂ ሰዎች..መሪዎች እና የሙዚቃ ባለሙያዎች ይገኛሉ፤የሙዚቃ ዝግጅትም ይኖራል፤ገቢዉ ለባለሜዳዉ ቡድን ቡና ይሆናል፤
ይሄ ቱጃር ከ15ቀናት በሁዋላ በአዲስ አባ ስታድየም ኢትዮጲያ ቡና እና ቲፒ ማዚምቤን ያጫዉታል፤የአፍሪካ ህብረት መዲና ስለሆነች አዲስ አበባ ለዚህ ጨዋታ ቦታነት ስትታጭ ብዙ ደጋፊ ያለዉ ክለብ በሚል ኢትዮጲያ ቡና በዉጭ ጉዳይ ሚንስትር ተመርጥዋል፤ዉድድሩ ጥቅምት 29 ይደረጋል፤ቲፒ ማዚምቤ የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫን ወስድዋል፤ዘንድሮ ደግሞ በኮንፌዴሬሽኑ የፍጻሜ ተፋላሚ ነዉ፤
የሁለቱን ጨዋታ የሚመሩት ዳኞች ኢትዮያዉያን ናቸዉ፤በነገራችን ላይ ተፒ ማዚምቤዎች ኢትዮጲያዊዉን ዳኛ ዘካርያስን በሴካፋ ክለቦች ጨዋታ መተዉታል፤ሜዳዉ ዉስጥ ሮጦ አመለጣቸዉ እንጂ ብዙ ለካልቾና ለቡጢ የተዘጋጁ ተጫዋቾች ነበሩ፤ይህ የሆነዉ ከ2 አመት በፊት ነዉ፤የነሱ አሰልጣኝ የነበረዉ ዲዮጎ ጋርዚያቶ ነበር፤መቸስ ዘካርያስ እንዳያጫዉተን አይሉም….እሱስ ምን ያስብ ይሆን በሜዳዉ ሲያያቸዉ???

በኢትዮጵያ ከግማሽ ክ/ዘመን በላይ የቆየ ማንዴላን የተመለከተ የደህንነት ሚስጥር ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ ከግማሽ ክ/ዘመን በላይ የቆየ ማንዴላን የተመለከተ የደህንነት ሚስጥር ይፋ ሆነ።ሚስጥሩን ማንዴላም እስካሁን ድረስ አይውቁትም።
የማንዴላ አሰልጣኝ ጄኔራል ታደሰ እና ኔልሰን ማንዴላ ኔልሰን ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ የፀረ-አፓርታይድ (የዘር-መድሎ) ተዋጊ አርበኛ መሆናቸው ይታወቃል።ለእስር የተዳረጉት ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና ወስደው እንደተመለሱ ነበር። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ 1962 ዓም ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው በወቅቱ ለማንዴላ ኢትዮጵያ ፓስፖርት በመስጠት አጋርነቷን የገለፀች ብቸኛ ሀገር ነበረች።

ከዘመናት በኃላ ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ወቅት የግድያ ሙከራ ተደርጎ እንደነበር ሚስጥሩን ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ ይዘው የቆዩ በቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ዘመን የኢትዮጵያ ፖሊስ መኮንን ዛሬ ጥቅምት 15/2006 ዓም ለመጀመርያ ጊዜ በሸገር ራድዮ የዜና እወጃ ላይ ገልፀዋል። ሻምበል ጉታ ዲንቃ በንጉሡ ዘመን የፖሊስ መኮንን ነበሩ። ማንዴላን በከፍተኛ ሚስጥር እንዲጠብቁ ኃላፊነት ከተሰጣቸው ጄኔራል ታደሰ(የማንዴላ አሰልጣኝ በወቅቱ ኮ/ል የነበሩ)፣ኮ/ል ፍቃደ እና ሻምበል ፈቃደ ውስጥ ነበሩ።ዛሬ የ76 አምቱ የእድሜ ባለፀጋ ሻምበል ጉታ ዲንቃ ለሸገር ሲናገሩ እንዲህ አሉ። '' ማንዴላን እንድጠብቅ ኃላፊነት የተሰጠኝ እኔ ነበርኩ።ማንዴላ የሚያድሩበት እና ወታደራዊ ስልጠና የሚወስዱበት የኮልፌ የፖሊስ ማሰልጠኛ ቦታ በተለይ እርሳቸው የሚገኙበት ቦታ 'የፈንጅ ወረዳ' ነበር የሚባለው።ከአራታችን በቀር ማንም ወደ እርሳቸው ቦታ ዝር ማለት አይችልም። ሲተኙ መስኮት ከፍተው ነው የሚተኙት።አንድ ቀን ታድያ አብሮኝ ከሚሰራው የፖሊስ ባልደረባዬ በጥብቅ እንደሚፈልገኝ ነገረኝ።ጣይቱ ሆቴል ተቀ...ጣጠርን እና ሃሳቡን ገለፀልኝ።'' ካሉ በኃላ አሁን አዲስ አበባ ላፍቶ አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ሻምበል ጉታ በመቀጠል እንዲህ ብለዋል- ''ጣይቱ ሆቴል የወሰደኝ ሰው ለጊዜው 2000 ፓውንድ በወቅቱ አስቡት 2000 ፓውንድን እና ሰጥቶ እንዲህ አለኝ- 'ሁለት ዕድል ከፊታችን ተቀምጧል።ሊያመልጠን አይገባም።ከፍተኛ ገንዘብ እናገኛለን።ቀጥሎም ወደ ውጭ ሀገር የመሄድ ዕድል አለን።ከአንተ የሚጠበቀው ማንዴላ በተኛበት ዛሬ ሌሊት በመስኮት ገብተህ በገመድ አንቀህ ግደል እና ውጣ እንደወጣህ መኪና ተዘጋጅቶ ይጠብቅሃል ከእዚህ

የውትድርና ሕይወት እንገላገላለን' አለኝ። እኔም ጉዳዩን ከሰማሁ በኃላ በጉዳዩ የተስማማሁ መስዬ ቀጥታ ለጀኔራል ታደሰ ነገርኩኝ። ጉዳዩ በሚስጥር ተይዞ ይህንን ያደረጉት ሰዎች ተደረሰባቸው እና ከሀገር እንዲወጡ(እንዲባረሩ) ተደረጉ ይህ ሚስጥር ለዘመናት ከእኔ ጋር የኖረ ነው።ጉዳዩን ማንዴላም አያውቁትም።'' ብለዋል። Image ኢትዮጵያ ለኔልሰን ማንዴላ የሰጠቻቸው ፓስፖርት ኔልሰን ማንዴላ በወቅቱ እንደ ሻምበል ጉታ ዲንቃ አይነት ታማኝ የኢትዮጵያ የፖሊስ መኮንን ባይገጥማቸው ኖሮ የደቡብ አፍሪካ የነፃነት ታሪክ ሂደትም ሆነ የነፃነት ትግሉ ታሪክ ሌላ መልክ በያዘ ነበር።ይህ ጉዳይ እጅግ ትልቅ ጉዳይ ነው።የኢትዮጵያ ፖሊስ ለአፍሪካ ያደረገው አስተዋፆ የሚያጎላ፣ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪክ ያደረገችው ትልቅ አስተዋፆ በመሆኑ በኢትዮጵያ የዜና አገልግሎቶች ሁሉ ትኩረት ተሰጥቶት የዓለም አቀፍ የዜና ሽፋን እንዲያገኝ ጥረት ማድረግ ለኢትዮጵያ ፋይዳው ብዙ ይመስለኛል። በመሆኑም ቢያንስ ለሻምበል ጉታ ዲንቃ የኢትዮጵያ ፖሊስ ጠርቶ ከማዕረግ እስከ ሽልማት ከእዚህ ባለፈም ጋዜጣዊ መግለጫ መስጠት እና ማንዴላ በሕይወት ዘመናቸው ሳሉ ሻምበል ጉታ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ሄደው እንዲያገኙዋቸው ማድረግን ሁሉ ይጠይቃል።ጉዳዩ የደህንነት ሚስጥር የነበረ በመሆኑ በወቅቱ ግድያውን ሊፈፅም የሞከረው አካል ወይንም ሀገር (ማንነቱን ሻምበል ጉታ አልገለፁም (የተባረሩት ዜጎች የየት ሀገር እንደነበሩ አልገለፁም) ዛሬ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ለሚኖረው ግንኙነት ጥላ እንዳያጠላ ስጋት ስለሚሆን ዜናው በተፈለገው ደረጃ ለዓለም ሕዝብ እንዳይደርስ የሚደረጉ ስውር ስራዎች እንደማይጠፋ ማጤን ሌላው ሥራ ሊሆን ይችላል። ማንዴላ ከእስር እስኪፈቱ ድረስ በኢትዮጵያ ፓስፖርት ነበሩ።ይህ የደቡብ አፍሪካ ፓስፖርት ከእስር በተፈቱ በ 8ኛ ቀን ያገኙት ነው።

“ለዋልያዉ ልጫወት”…በቻምፕዮንስ ሊግ የተጫወተዉ ዋሊድ አታ


ይህ ከዋሊድ አታ የስዊድኑ ሂልስነቦርግ ተከላካይ ለTeam Ethiopia የfacebook pageየተላከ ደብዳቤ ነዉ፤ተጫዋቹ በዩሮፓ ሊግ እና ቻምፕዮንስ ሊግ ተጫዉትዋል፤ለዋልያዉም ለመጫወት ፍላጎቱን የገለፀዉ ከናይጄሪያ ጨዋታ በፊት ቢሆንም ከዋልያ በኩል ምንም ምላሽ አላገኘም..ከዚህ ደብዳቤ ጋር አብሮ የተጫዋቹን እንቅስቃሴ የሚያሳይ ምስል አለ..እናም እናንት የዋሊድን ጥያቄና ምስሉን አይታችሁ ትፈርዱ ዘንድ እነሆ!!!
My name is Walid Atta, born in Riyadh in Saudi Arabia in August 28th 1986. My career as a professional football player started in early 2008 when I joined team AIK in Stockholm Sweden. Team AIK was founded in 1891 (122 years ago) and is measured as top club in the Swedish league for decades. During my engagement with AIK (3 years) I gained a lot of experience in all aspect of professionalism as a football player. Throughout these years a became a key player and performed very well in many games in the league also in some international games as well. These 3 successful years became my key to the Swedish national team of U21 and many offer from international clubs, like Glasgow Rangers from Scotland, Valencienne from France and Dinamo Zagreb from Croatia and a few more. After consulting family and my agent I decided to sign up for Dinamo Zagreb from Croatia. Less successful journey with injuries and unstable club economy leading to the club not been able to pay players’ salaries.  Subsequently free ticket from Dinamo Zagreb to leave the club and sin up for any other club with no obligation what so ever.

Helsingborg IF, Swedish football clublocated in a city of  Helsingborg. the club was previous year champions of Swedish league which means Europa Champions League qualifications games to be played if I signed up for the club which I did. Successful story again many international games like hanover 96, Levante and Twente , 7 goals as a center back more than any defender in the league, many offers from clubs in Europe, and voted to be player of the year.

I  have been following the Ethiopian national team in African cup and world cup qualification and I am so impressed and proud how they are progressing just getting better and better It looks good and promising for Ethiopian football in future and hopefully I can be a part of that team and contribute to an even greater success, that would be a fantastic honor.

Kind Regards
Walid Atta

የኢትዮጲያ እግር ኳስ: በስሜትና በእዉነት መካከል!


“ከታሪክ መማር የማይፈልግ ሰዉ ታሪካዊ ስህተትን ለመድገም የተረገመ ነዉ”
በሰኢድ ኪያር
እንደመግቢያ
አሁን ሰማይ የተሰቀሉ ስሜቶች ቀዝቅዘዋል፤በጭፍን ዋልያዉን ከማሞገስና ከመስቀል በእዉነታዎች ላይ መወያየት ተጀምርዋል፤በመጀመሪያዉ ጎን ደግሞ ናይጄሪያን በመልስ ጨዋታ ስለማሸነፍ መዘመሩን ቀጥልዋል፤ይህ ሚድያዉን ያጠቃለለ ፉከራ ከጥቅምት 3ቱ በጥቂት ግን ወሳኝ ነገር ለየት ይላል፤ቢያንስ ቢያንስ ”እንዴት???” የሚለዉን ቀም ነገር ማካተት ጀምረዋል፤ይህ ጽሁፍም ያልተስተዋለዉን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ስሜት ዝብርቅርቅ ይዳስሳል..ከእዉነት ይልቅ ስሜትን ስለተከተሉት ወቅቶች………
የዛን ቀን ደስታ ልዩ ነበር፤ከዳሪሰላም ታንዛኒያ ሲቃ የተሞላባቸዉ ድምጾች የኢትዮጲያን ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ አበሰሩ፤ለእግር ኳሱ ትንሳኤ ቀን እንደሆነም በመነገሩ አዲስ አበባ እና መላ ኢትዮጲያም ተነቃንቀዋል፤በለንደን ኦሎምፒክ ወንዶቹ ሲያቅታቸዉ እንስቶቹ ግን የተለመደዉን ወርቅ አምጥተዉ ህዝቡን አኩርተዋል፤እናም በእግር ኳሱ የዉጤት ማማ ሴቶች ነገሱበት፤”የሴቶች እግር ኳሱ መነቀቃት”ም በይፋ ተነገረ!!በየመንገዱ ሉሲ– በየራድዮ ጣቢያዉ- ጋዜጦች እና የቲቪ መስኮቶች የሉሲ ገድል ዝማሬ ጣሪያዉን ነካ፤ሉሲዎቹ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፋቸዉ ይበል የሚያሰኝ ነገር ነዉ፤እንዴት አለፉ የሚለዉ ግን በሞራልና በጮቤ ረገጣዉ መሀል ተሸሽገዉ ቦታ አላገኙም፤ሁሉም ቀርቶ ሉሲዎቹ ከዚህ በፊት ለአፍሪካ ዋንጫ ባለፉባቸዉ ዉድድሮች እንኩዋን ምን ገጠማቸዉ የሚለዉን ማየት አልተቻለም፤አላማችን ለአለም ዋንጫ ማለፍ ነዉ—ስሜት የነገሰበት የሁሉም የርእይ ስንቅ ነበር፤ ዉድድሩ ሲጀመር ግን ይህ ሁላ የስሜት ሰቀላ ዉሀ ተቸለሰበት፤ከመጀመሪያዉ ደቂቃ አንስቶ ኮትዲቫሮች ግብ ማምረት ጀመሩ፤5-0 ጨዋታዉ አለቀ፤እዚህ ላይ ቡድኑ ልምድ የለዉም እንዳይባል 3ተኛ የአፍሪካ ዋንጫቸዉን የሚጫወቱ–ለ2ተኛ ጊዜ ሉሲን በአህጉሪቱ መድረክ የሚወክሉ…በተለያዩ ማጣሪያዎች ልምድ ያላቸዉ ተጫዋቾች የተሰባሰቡበት ቡድን ነዉ፤ግን አልቻለም፤ያቃተዉ ደግሞ የኮትዲቫሮችን ማጥቃት ማቆም ብቻ አይደለም መሀል ሜዳዉን አልፎ መሄድ የዳገት ያህል ለሉሲዎቹ ከበደ፤ናይጄሪያ ቀጣዩን ጨዋታ 3-0 ረታች፤ከካሜሩን ጋር 0-0 የሉሲዎቹ መጨረሻ ከ8ቱ ቡድኖች 8ተኛ ..ብዙ ግቦች ያስተናገዱ ግን አስደንጋጭ ሙከራ እንኳን ያላደረጉ ሁነዉ ተሸኙ፤ከምንም በላይ ‘’ተነቃቃ’’ የተባለዉ እግር ኳስ አሸለበ፤የያኔዉ አይነት ጎሮ ሸባዮ አሁን በሉሲዎቹ አከባቢ የለም፤አርቴፊሻሉ መነቃቃት በክለቦች የዋንጫ ጨዋታ እንኳን አይኖችን መግዛት አልቻለም፤”ብዙ ትምህርት አግኝተንበታል “–የተለመደዉ ሽንፈት ሰራሽ መልስ ተከተለ፤ ይህ ከሆነ 1 ድፍን አመት ሁኖታል፤ስለ ሉሲ ያኔ የተዘመረዉን ያህል አሁን ስለ ሉሲ የሚያወራም የለም፤እንደእምቧይ ካብ በሚናዱ የስሜት ዝብርቅርቆች መሀል ከተገኙት የኢትዮ ቡድኖች አንዱ ሆኑ ..ሉሲዎች ዋልያ…. ከኢትዮጲያና ሱዳን ጨዋታ በፊት–ግዮን ሆቴል –“የኢትዮጲያ እግር ኳስ እንዴት ከወደቀበት እናንሳ?’’ በሚል ጥናታዊ ጽሁፍ ቀረበ፤ፌዴሬሽኑ ነዉ የጥናት ባለቤቱ..እናም ከትምህርት ተቋማት የተዉጣጡ ዶክተሮችም ሳይቀሩ ተሳትፈዉበታል፤ማጠቃለያዉ –የኢትዮጲያ ኳስ እንዲያድግ መሰራት የሚገባቸዉ ነገሮች ተብለዉ…. –አደረጃጀትን ዘመናዊ ማድረግ —-ፕሮጀክት በስፋት እንዲኖሩ –ወጥ ስልጠና ማንዋል ማዘጋጀት —አካል ብቃት ላይ በሚገባ መስራት..ወዘተ…. በሚል ጥናቱ አስቀመጠ፤ለዚህም ተሰብሳቢዉ ማረጋገጫ ቃሉን ሰጥቶ ተለያየ፤ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮች ለመፍታት ቢያንስ ቢያንስ አመታት ይፈጃሉ፤አጥኚዎቹም ሆኑ ተሳታፊዎቹ ይህንን ነገር አላምጠዉ ሣይጨርሱ ዋልያዉ ለአፍሪካ ዋንጫ አለፈ፤እዚህ ላይ ሁነኛ መነጋገሪያዎች መነሳት ይገባቸዉ ነበር፤ወይ ጥናቱ ፉርሽ ነዉ!! አልያም ጥናቱ ትክከል ሆኖ ቡድኑ በአጋጣሚ አለፈ፤ካልሆነም ደግሞ ጥናቱ እንደችግር ያስቀመጣቸዉ ሀሳቦች እንዳሉ ሆነዉ ጠንካራ ለአፍሪካ ዋንጫ የሚያልፍ ቡድን ሊሰራ ይችላል….!!.ስሜት መር የሆነዉ እግር ኳሱ ግን ጆሮ ዳባ ብሎ ጉዞዉን ቀጠለ! ቤኒን ጋር አቻ..ሱዳንም ጋር አቻ ወጥቶ ዋልያዉ ደቡብ አፍሪካ ደረሰ፤ይህ በርግጥም ከታሪክ አንጻር ትልቅ አጋጣሚ ነዉ፤ግን ከስሜት ምህዋር ያልወጣ ያለጊዜዉ የደረሰ አልያም የማይደገም ስለመሆኑ ማሳያዉ በዉድድሩ ላይ የታየዉ ቡድን ነበር፤”ዋንጫ እንደርሳለን—ባይሆን እንኳን 4ቱ ዉስጥ ከገባን በቂያችን ነዉ!!”የሚል እቅድም ተነድፎ ነበር፤ ከዛምቢያ ጋር አቻ የወጣዉ ቡድን ሜዳ ላይ ባሉ መነጻጸሪያዎች ሁሉ(ካርድንም ሳይጨምር) ተበልጥዋል፤በስሜት በሚነጉደዉ እይታ ግን ይህ ቡድን የአፍሪካ ባርሴሎና ተባለ፤ቀጠለና በቡርኪና ፋሶ ሙሉ የጨዋታ ብልጫ እናም 4ት ግቦች አስተናገደ፤በስሜት የተወጠሩት ልቦች አሁን ተንፈስ አሉ፤ናይጄሪያም ብልጫዉን ወስዶ 2-0 አሸነፈ፤ከተሳታፊ ቡድኖች በአነስተኛ ነጥብ በአነስተኛ ሙከራ እናም በብዙ ግቦች በማስተናገድ ግምባር ቀደም ሁኖም ተመለሰ፤”እንደጀማሪ የነጻ ትግል ተፋላሚ”!!! ይህ ነገር በዚህ ትዉልድ ብቻ የተከሰተ አይደለም፤እግር ኳሱ— ከዚህ በፊት የነበሩት ቡድኖች አንዴ ብልጭ ካዛም ድርግም በሚሉ ዉጤቶች ተጭበርብሮ በግድ የኢትዮጲያን እግር ኳስ ትንሳኤ መስክሯል፤
አዘናጊዎቹ ድሎች
3ተኛዉ የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጲያ ትልቁ ታሪክ ነዉ፤ሉቻኖ ቫሳሎ ከንጉሱ እጅ ታሪካዊዉን የአፍሪካ ዋንጫ ከተቀበለ ወዲህ ማንም ኢትዮጲያዊ ያንን መድገም አልቻለም፤ይሔ ድል ለያኔዉ ትዉልድ ብቻ ሳይሆን” ኳስ ድሮ ቀረ” ለሚለዉ መካካለኛዉ የእግር ኳስ ዘመን ሰዎችም እንደማሳያ ይቆጠራል፤የያኔዉ ድል እንዴት ተገኘ?የሚለዉን ዋነኛ ነገር ያልመረመረዉ ትዉልድ ለተከታታይ ዉድቀቶቹ ምክንያት እስኪያጣ ድረስ ግራ ተጋብትዋል፤አስኪ ዋንጫ የበላ ቡድን እንዲህ አይነት የሽንፈት ጉዞ ሲከተለዉ ምን ይባላል፤—ዉጤት ያመጣበትን ምክንያት አለማወቁ ከማለት ዉጭ!!!ተከታዩ ዉጤት ታሪካዊዉ ድል አድራጊ የኢትዮጲያ ቡድን የአፍሪካን ዋንጫ ካነሳ በሁዋላ ባሉት አመታት ያስመዘገባቸዉ ዉጤቶች ናቸዉ!! ከ4ተኛዉ እስከ 13ተኛዉ የሊቢያ አፍሪካ ዋንጫ 6ት ዉድድሮችን ተካፍሎ..ካደረጋቸዉ 19 ጨዋታዎች 14ቱን በሽንፈት 1ዱን አቻ 4ቱን በማሸነፍ አጠናቅዋል፤41 ግቦች አስተናግዶዋል 20 ብቻ አስቖጠወርዋል..21 እዳ ማለት ነዉ ሲወራረድ፤ያስከበረዉ የበላይነት አልያም ያስጠበቀዉ ክብርም አልነበረም፤ጭራሽኑ ከ13ተኛዉ በሁዋላ 31 አመታት እልም ብሎ ጠፍትዋል፤መነቃቃትን ፈጥሮ የነበረዉ ቡድን የተከተለዉ ታሪክ እንግዲህ ይህ ነዉ!!!! ነገርየዉ ይቀጥላል፤የሲካፋ ዋንጫ በኢትዮጲያ ለመጀመሪያ ጊዜ ተዘጋጅቶ ኢትዮጵያ ዋንጫ አነሳች..ጎሮ ወሸባዉ ቀልጦ በቀጣይ ሽንፈቶች ደግሞ እንደበረዶ መቅለጥ ተከትለዋል፤የክለቦችም ወግ ቢሆን ከዚህ እላፊ አልሄደም፤ አለም ዋንጫ… “ አርጀንቲና አትሄዱም”….. “አርጀንቲና አትሄዱም”…. የሚሉ የተስፋ መቁረጥ ድምጾች በአዲስ አበባ ስታድየም የተሰሙት በጋርዚያቶ ተመርቶ ለአለም ዋንጫ ባለፈዉ የወጣት ቡድን ላይ ነበር፤በህዝብ እና በካፍ ቀና እርዳታ ወደ አለም ዋንጫዉ ማለፉን ያረጋገጠዉ ወጣት ቡድን በጥሎ ማለፋ በአንጎላ 5-2 በደረጃ ጨዋታ በግብጽ 2-0 በጨዋታ ብልጫ ጭምር ሲሸነፍ ህዝቡ ወደ አለም ዋንጫ የማለፍ ትርጉም አልባ መሆኑን በማሰብ ነዉ.አርጀንቲና አትሄዱም ያለዉ!! አሁን ከ13 አመታት በሁዋላ የያኔዉን ለአለም ዋንጫ ያለፈ ቡድን ስናየዉ በርግጥም ተመልካቹ ትክክል እንደነበር ማረጋገጥ እንችላለን፤ቡድኑ እንደምንም ማጣሪያዉን አልፎ(ከ5ጨዋታ 1ዱን በልዩ ህግ አሸንፎ) በአለም ዋንጫዉ በታናናሾቹ 3ቱንም ጨዋታ ተሸንፎ ተመለሰ፤(ከ8 አንድ አሸንፎ ማለት ነዉ)!ወጣት የተባሉቱ በዋናዉ ቡድን ይህንን መድገም አልቻሉም፤ጭራሽም ለረጅም አመታት ለመጫወት የበቁት ጥቂቶቹ ብቻ ናቸዉ፤ እዚህ ላይ ዋናዉ ነገር ተጫዋቾቹ ያገኙትን ድል ማንኳሰስ አይደለም፤ለሁሉም ኢትዮጲያን በአለም ዋንጫ ለወከሉ..ማጣሪያዉን ለተጫወቱ..ላሰለጠኑ ላገዙ—ለሁሉም ትልቅ ክብርና ምስጋና ሊቸር ይገባል፤ዋናዉ ቁም ነገር ግን የያኔዉ ድክመት ለዛሬዉ ማስተማሪያ ስለሚሆን ዋነኛ ድክቶቹን ነቅሶ ማዉጣት ነዉ፤እናም ኢትዮጲያ ዛሬ ላይ ሁና የዛሬ 13 አመት ለአለም ዋንጫ ያለፈዉ ቡድንዋ ምን እንደጠቀማት መናገር አለመቻልዋ ነዉ! አለም ዋንጫን ማለፍ ሁነኛ ጥቅም ከሌለዉ የወራት ሆይ ሆይ ሆይታ እናም ቀጥሎ ሀዘን የሚያስከትል ከሆነ ዋጋ ቢስነቱ ያይላል!!በተደጋጋሚ የመሳተፍ የሚያስችል ቁመና ያለዉ ጠንካራ ቡድን ከሆነ በሴካፋ ዉድድርም ቢሆን ጥንካሬዉ ሲገነባ ለነገ ተስፋ ይሠጣል፤
የአሁኑ ዋልያ…
የላይኛዎቹ መነሻዎች አሁን ካለዉ ቡድን ጋር ለማያያዝ ጠቃሚ ይሆናሉ፤የዋልያዉ የአፍሪካ ዋንጫ ሂደት ሲገመገም ከማለፍ በስተቀር በዉድድሩ ላይ ያሳየዉ ነገር ጠንካራ እንዳልሆነ ምስክር አያስፈልገዉም፤ከዛ በሁዋላ ባደረጋቸዉ የአለም ዋንጫ ጨዋታዎችም ቦትስዋናን እና ሴንትራል አፍሪካን በደርሶ መልስ ደቡብ አፍሪካን አዲስ አበባ ላይ ማሸነፍ ቢችልም ጨዋታዎቹ ለቡድኑ ጥንካሬ ምስክር መሆን አልቻሉም፤አዲስ አበባም ላይ ሆኑ ዉጭ የተደረጉቱ ጨዋታዎች አስጨናቂ ነበሩ፤የጨዋታዎቹ ፍጻሜ ፊሽካ እስኪነፋ ድረስ ደረትን ነፍቶ የቡድኑ ጠንካራ ነገር ይህ ነዉ ለማለት አዳጋች ነበር፤የተጋጣሚዎች መቅለል–ማለትም እንደከዚህ ቀደሞቹ ቡድኖች አይነት የነ ግብጽ-ካሜሮን–ቱኒዚያ አይነት ጠንካራ ቡድኖች ጋር አለመጫወቱ–እንዲሁም በዉጤት ደረጃ ጥሩ ባይሆንም በማሸነፍ እድለኛነት እዚህ ደርስዋል ቀደም ብለን እንዳየናቸዉ ቡድኖች አንዴ ታይቶ ብን ብሎ የሚጠፋ ክስተት እንዳይሆን አሁን ላይ ያሉትን ህጸጾች ነቅሶ ማዉጣት ግድ ይላል፤ዋልያዉ የዛሬ 2ት አመት ከተሳተፈበት ሴካፋ ጀምሮ ተጋጣሚን እንዴት እንደሚቀርብ ለማወቅ ከባድ ነዉ፤በአብዛኛዉ ከአሰልጣኞቹ እንደሚሰማዉም..ተጋጣሚ ከተከላከለ የሚያጠቃ— ካጠቃ ደግሞ የሚከላከል ስለመሆኑ ነዉ፤ይህ ነገር ማሸነፍን እንዴት እንደሚመጣ አልያም ሽንፈት በምን ምክንያት እንደመጣ የሚያስተምር አይደለም፤ቄሱም መጽሀፉም ዝም ብሎ ከመቀጠል ዉጭ! የአሁኑ ዋልያ አጨዋወት ግምት ላይ የተመሰረተ ረጅም ኳሶችን አዘዉታሪ መሆኑ በጨዋታዎች ላይ ተመልክተናል፤ይህ ደግሞ አሁን አለም እየተቀየረበት ካለዉ አጨዋወት በሚልየን ምይሎች ርቀት ላይ ያስቀምጠዋል፤ተከላካዮች ኳስን ተጫዉቶ ከመዉጣት ይልቅ በረጅሙ ጠልዞ እንደገና የመጠቂያ ምንጭ እንደሆኑ በተደጋጋሚ አይተናል፤አማካዩ ክፍል ለፈጠራ ዝግ ነዉ፤አለም ትቶት የወጣዉን በተከላካይ አማካዮችን አብዝቶ ያለጨዋታ አቀጣጣይ አነስተኛ ፈጠራ ያላቸዉን ተጫዋቾች መጠቀም የአሁኑን ዋልያ መሀል ሜዳ እጅጉን ደካማ ያደርገዋል፤3ት ቅብብል ለማድረግ የሚቸገር አማካይ ክፍል በንጽጽር ጥሩ ለሚባሉት አጥቂዎች የሚያበረክተዉ አስተዋጽኦ ኢምንት ነዉ፤በዚህ ቦታ በተደጋጋሚ የአሰልጣኞች ምርጫ ያልነበረዉ ሽመልስ በቀለ ለብቻዉ ኢትዮጲያ ምን አይነት ተጫዋቾች እንደሚያስፈልጋት የሚያሳይ ሁኑዋል፤ እነዚህና እና መሰረታዊ የሚባሉ የቡድን ዉህደት ችግር ያለበት ዋልያ ከምንም በላይ አቆለጳጵሶ፤ከአቅሙ በላይ አወድሶ፤የህዝብን ስሜት አንሮ በስተመጨረሻ አሸማቃቂ አይነት ብልጫ ሲመጣ ምክንያት መደርደር ብልህነት አይሆንም፤ብዙዎች ዋልያዉ ነገ ከሚያደርገዉ ጨዋታ በፊት የወዳጅነት ጨዋታ አለማድረጉ እንደሚጎዳዉ ይናገራሉ፤ነገር ግን ዋልያዉ እስካሁን ካሸነፈባቸዉ ጨዋታዎች ምንም አይነት ድክመት ለማሻሻል ሳይችል ሌላ ጨዋታ ማድረግ ትርጉም አልባነቱ ይጎላል፤ አርቆ ማሰብ በዋልያዉ አከባቢ መኖሩ እጅግ አስፈላጊ ነዉ፤ናይጄሪያን ማሸነፍ ይቻላል፤አለም ላይ ያለን ጠንካራ ቡድንንም እንዲሁ…ነገር ግን ምንም ጥንካሬ ሳይኖር ትልቁን ሆነ ትንሹን ቡድን ማሸነፍ ዋጋቢስ ነዉ፤ከዚህ በፊት የነበሩት ድንገቴ ቡድኖች እንዳመጡት የሚረሳ ዉጤት ከመመስከር በስተቀር!!
ናይጄሪያ…የኋላን ማስተዋል….
ስለ ናይጄሪያ ጨዋታ ሲነሳ ሰዎች የኋላን ማየት አስፈላጊ አለመሆኑን ሲናገሩ ነበር፤ምክንያቱም ናይጄሪያ ምን ያህል በሽንፈት እንዳቆሰለን ስለሚታወቅ…ነገሩ ግን ህልም ተፈርቶ….እንደሚባለዉ ነዉ፤ናይጄሪያ በልጦ እስከዛሬ አሸንፎናል፤ይህ ሀቅ ነዉ..ዛሬም ቢወራ ከታሪክነት ባለፈ ለምን እንደበለጠን መማሪያ ይሆናል፤ትላንት የበለጠበትን መንገድ የያኔ ተጫዋቾች (አሁን በአሰልጣኝነት እና ዙሪያዉ ያሉ) በሚገባ አስረድተዉ አሁን ዋልያዉ እንዴት መብለጥና ማሸነፍ እንዳለብን ማስረዳት ይችላሉ፤አለበለዚያ ግን የኋላን ትቶ አልያም ማንሳቱን ፈርቶ የአሁኑን ብቻ ማሰብ ጎዶሎነት ይሆናል፤ጸሀፊዉ ዳንኤል ክብረት እንዳስቀመጠዉ…. ’’ከታሪክ መማር የማይፈልግ ሰዉ ታሪካዊ ስህተትን ለመድገም የተረገመ ነዉ፤እንዲህ የሚያደርግ ግን እንስሳ ብቻ ነዉ፤እንስሳት ታሪክ የላቸዉም፤ታሪክ ስለሌላቸዉ የዛሬ 1ሺ አመት አንድ በሬ የሰራዉን ስህተት የዛሬዉ በሬ ይደግመዋል፤የዛሬ 3 አመት አንድ በግ የሰራዉን ስህተት ዛሬም ያዉ በግ ሊሰራዉ ይችላል፤የዛሬ 600 አመት ምድርን ስትጭር የነበረችዉ ዶሮ ዛሬም እንደምትጭረዉ ማለት ነዉ፤ዶሮዋ ለመጫር ነዉ እንጂ ለመብረር ልታስብ አትችልም፤ሰዉ ግን ከዚህ ዉጭ ነዉ፤ሰዉ ከትላንት ይማራል..ስህተቱን ያርማል……ስለዚህ የሰዉ ልጅ የትላንቱን ጥሩ ይዞ እንዲቀጥልና መጥፎዉን እንዲያርም የጎበጠዉን እንዲያቀና…ተብሎ የታሪክ ትምህርት የሚሰጠዉ..’’
ከስሜት ወደ እዉነት…
ኢትዮጲያ እንድታሸንፍ የማይፈልግ የለም፤አስተማማኝ ቡድን ቢኖራት ምን ግዜም የምትታወቅበት ጥንካሬ ብታሳይ የሁሉም ምኞት ነዉ፤ነገር ግን ነገ በማይደገም አካሄድ ቡድንዋ በዉጤት ሲደለል ዝም ማለትም ተገቢ አይሆንም፤ዉጤት ያመጡ ሰዎች ክብር ይገባቸዋል፤ሽልማትም ቢጎርፍላቸዉ አስፈላጊ እና የሚበረታታ ነዉ፤ነገር ግን ዉጤት ያመጡበትን መንገድ መመርመር ደግሞ እዉቅና ከመስጠት የተለየ እይታን ይጠይቃል፤ጥሩ ያልሆነን ቡድን እላይ ሰቅሎ ሲፈጠፈጥ ከመሳቀቅ ከመነሻዉ እያሸነፈም ቢሆን በድፍረት ስህተቱን መጠቆም አስፈላጊ ነዉ፤ የባለፈዉ ሳምንት ጨዋታንም በዚህ መነጽር መቃኘቱ ጠቃሚ ነዉ፤የመጀመሪያዉ ነገር ከጨዋታዉ በፊት ይነገሩ የነበሩ የሁለቱ በድኖች ልዩነቶች አሁንም እንዳሉ ተረጋግጥዋል፤ናይጄሪያ በኬሺ የተጫዋችነት ዘመን የመንግስቱ ወርቁን ቡድን በአካል ብቃት ጥንካሬ እንደበለጡት ዛሬም የሰዉነትን ቡደን ከ30 አመታት በሁዋላም በልጠዋል፤ይህን ነገር ከእኔ ከጻሀፊዉ..ከናንተ አንባቢዎቸ እና ከአሰልጣኞች በላይ ተጫዋቾቹ ያቁታል፤ሁሌም በተደጋጋሚ ይናገሩታል፤ለዚህም ይመስላል ያለወትሮዉ በግምት ይላኩ የነበሩ ኳሶች የቀነሱት…ተጫዋቾቹ ኳስዋን በሚችሉት መንገድ በመሬት በአጭር ቅብብል ለመብለጥ ጥረዋል፤ከሌላዉ ጊዜ በተለየም ከተከላካዮቹ ደፍሮ የሚቀበል አማካይ ብቅ ብልዋል፤እሱም አዳነ ግርማ ነዉ፤የዋልያዎቹን ልምምድ ላለፉት 2ት አመታት በቅርበት ስከታተል የኳስ ብልጫን ለመዉሰድ የሚያስቸል ልዩ ስልጠና አላየሁም፤እናም አዳነ እና ጓደኞቹ ያደርጉ የነበሩት እንቅስቃሴ በትሬኒንግ የተነደፈ ስላለመሆኑ የቅብብላቸዉ መጨረሻ ያሳብቃል፤ለ6ት በራሳቸዉ ሜዳ ይቀባበላሉ..ከዛም በግምት ኳሶች ይጣሉና አጥቂዎቹ አላስፈላጊ ድካም ዉስጥ ይገባሉ፤ያም ቢሆን ግን ናይጄሪያን በፈለገዉ መጠን እንዳይንቀሳቀስ አድርገዋል፤የዚህ ነገር መነሻ የሆነዉ ተጫዋች በጊዜ ከተቀየረ ደግሞ ከርሞም ይህ አይነቱ አጨዋወት ተፈላጊ አለመሆኑን ያሳያል፤አሰልጣኝ ሰዉነት ከጨዋተዉ በሁዋላ ከአንድ ሬድዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ..”አሁን ጊዜዉ የመጫወት ነዉ፤ተጫዉቶ ማሸነፍ ያስፈልጋል፤ይህንንም ለመተግበር ሞክረናል” የሚል አንደምታ ያለዉ አስተያየት ሰጥተዋል ፤የመጀመሪያዉ ነገር መጫወት ከተፈለገ..እናም በመጫወት ብልጫ መዉስድ እንደሚቻል ከተረጋገጠ መጫወት የሚችሉ ተጫዋቾችን ለምን አልተካተቱም ?ይሆናል ጥያቄዉ…….ለማስረጃ ያህል መሀል ክፍሉን ለ90 ደቂቃ ተፈራርቀዉ ከተጫወቱት አስራት..አዳነ..አዲስ..እና ምንያህል ..ዉስጥ አንዳቸዉም በክለባቸዉ የጨዋታ አቀጣጣይነት ሚና ኑርዋቸዉ አያቅም፤አዳነ አጥቂ..አስራት እና አዲስ ቀሚ..ምንያህል የክንፍ ተጫዋቾች ናቸዉ፤እናም የመሀል ክፍል ብልጫ ያለመሀል ተጫዋች..ለዚያዉም የመፍጠር ብቃቱ ደካማ የሆነን ይዞ ማሰብ ከባድ ይሆናል፤ሀገሪቱ ደግሞ የአማካይ ተጫዋች ደሀ አይደለችም..ሌላዉን እንተወዉና የአዲስ አበባ ስታድየም መጫወቻ ሜዳ ሁሌም የመሀል ክፍሉ ሳር በቶሎ መበላት ለዚህ የማይናገር ምስክር ነዉ!!! ናይጄሪያ ጋር እንዴት መጫወት እንዳለብ እና እንዴት መጫወት እንደሌለብን በጨዋታዉ ታይትዋል፤የዚህ ቀን ችግር ግን የተጀመረዉ ዋልያዉ አሸናፊ ሆኖ ከማንም በላይ በተባለባቸዉ የቦትስዋና..ሴንትራል አፍሪካ..ደቡብ አፍሪካ ጨዋታዎችም ጭምርም ነበር፤በነዚህ ጨዋታዎች በየደቂቃዉ የሚጠልዝ..ኳስ ከእግሬ ዉጭልኝ በሚል መንፈስ የሚጫወት ቡድን ነበር፤ያም ቢሆን ግን ስላሸነፈ ከነስህተቱ ተንቆለጳጰሰ፤ድል ማድረግ እናም መመስገን በጣሙን ጥሩ ነገር ነዉ፤ነገር ግን ምንም ላይ ያልተመሰረተ ድል ነገ ምንም ላይ ሲጥል የናይጄሪያ አይነት ዱብ እዳ ያስከትላል፤
መፍትሄ…
ችግር የመፍትሄ ቁልፍ ነዉ፤እናም ኢትዮጵያ እግር ኳሴ አድግዋል ባለችበትም ሆነ በደከመችበት ጊዜ ያለመታከት የሚያሸነፍኑን የምእራብና ሰሜን አፍሪካ ቡድኖችን ለመብለጥ ወደ እዉነታዉ መምጣት አለብን፤”እኔ ጢቅ ጢቅ ጨዋታ የሚጫወት አልፈልግም.የሚጋጭ የሚፋለጥ እንጂ” የሚል አስተሳብ ያለዉ አሰልጣኝ ናይጄሪያም ሲመጣ ተጋጥቶና ተፋልጦ አሸንፎ ማሳየት ይኖርበታል፤አልያም ደግሞ አስቀድሞ በኳስ መብለጥ አለብን የሚለዉን መያዥ ይኖርበታል፤እኔ ይህንን የምጽፈዉ ላለፈዉ ቡድን አይደለም፤ከዚህ በኋላ ለሚመጣዉ ነዉ፤እንኳን አሰልጣኙና ባለሙያዉ ቀርቶ ተመልካቹ እንኳን ለይቶ ኳስ የሚጫወቱ የዉጭ ቡድኖችን የነፍሱ ያህል በሚወድበት ሀገር ለጥለዛ ና አካል ግዝፈት የሚሰጠዉ ትኩረት መቅረት አለበት፤እከሌ ምን ያህል ኳሶችን አጨናገፈ ሳይሆና እከሌ ምን ያህል ኳሶችን አስተካክሎ ሠጠ መመዘኛ መሆን አለበት፤፤ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ክህሎት ያልዋቸዉ ተጫዋቾች ሀገር መሆንዋ ለክርክር ማቅረብ ጉንጭ ማልፋት ነዉ፤አለምም በዚህ በዉብ እግር ኳስ ቅኝት እየተመራ መሆኑ ለእግር ኳሱ ትልቅ እድል ነዉ፤አለም ተጫዉቶ ስለማሸነፍ እያዜመ ነዉ፤ጀርመን ከጉልበት ወደ ጥበብ መንገዱን ጠርግዋል፤ስፔን እግር ኳሱን በአጭር ቅብብል መደብ አናቱ ላይ ከወጣች ቆይታለች፤ዋልያዉስ???አፍሪካን ለመቆጣጠር ጊዜዉ አሁን ነዉ!!ከፍለጠዉ ቁረጠዉ አጨዋወት ወደ ጭንቅላት ጨዋታ መቀየር..ለዚህ ደሞ በቂ ተጫዋቾች በኢትዮጲያ ይገኛሉ፤እናም ለዋልያዉ ትንሳኤ በመልሱ የካላባር ጨዋታ ሆነ በቀጣየቹ ዉድድሮች ይህንን መሞከሩ በእዉር ድንብር ከመሄድ በእዉቀት አለምን መከተልን ያስገኝለታል!!!!

Sep 9, 2013

የበቅሎ ጥያቄ ( By Daniel Kibret)

 ‹‹እንዴት አድርገው ነው የጨቆኑት፤ ለመሆኑስ የአንቺ አያቶች ስንት ናቸው? እርሱ የተነገረውን ብቻ ነው የሚያውቀው፤ ያልተነገረውስ? ከታሪካችንኮ በጣም ጥቂቱ ነው የተጻፈው፤ ከተጻፈውም በጣም ጥቂቱ ነው የተነገረው፡፡ ባልተጻፈው ታሪካችን ውስጥ ማን ምን እንደነበረ ማን ያውቃል? ለምሳሌ በሀገረ እሥራኤል አህዮች እጅግ የሚወደዱ የቤት እንስሳት ነበሩ፡፡ ነገሥታቱም፣ ካህናቱም፣ ነቢያቱም ዘመኑ ዘመነ ሰላም ሲሆን በአህያ ነው ይሄዱ የነበሩት፡፡ ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም የገባው በአህያ ነው፡፡ ድንግል ማርያም ወደ ግብጽ የተሰደደችው በአህያ ነው፡፡ በጥንታውያን ግብጾች ዘንድ አህያ የመኳንንትና የነገሥታት ሀብት ማሳያ ነበር፡፡ የናርማር ወይም  የሖር - አሃ መቃብር እንደሆነ በሚታመነው ቦታ ላይ በተደረገ ቁፋሮ አህዮች ከነገሥታቱ ጋር በክብር ተቀብረው ተገኝተዋል፡፡ በዚያ ጊዜ አህዮች የቤተ መንግሥቱን ምግብ እየተመገቡ፣ በቤተ መንግሥቱም እየተሸለሙ ኖረዋል፡፡ በሌላው ዘመን ደግሞ ይህንን ፈረሶቹ ወስደውታል፡፡››

‹‹ወደ ኋላ ተመልሰሽ ሁሉን እንስሳት ብታያቸው ታሪካቸው እንደዚሁ ነው ልጄ፡፡ በዘርሽ አትጨቁኝም፤ በዘርሽም አትጨቆኝም፡፡ የጭቆና መሠረቱ ኃይልና ሥልጣን ነው፡፡ አቤልን የገደለውኮ ቃየል ነው፡፡ የአንድ ማኅፀን ልጆች ናቸውኮ፡፡ ቃየል አቤልን የገደለው ለጥቅም ሲል ነው፡፡ እስኪ የሰዎችን ታሪክ እይው አፍሪካውያንኮ በራሳቸው በአፍሪካውያን ይጨቆኑ ነበር፡፡ ሥልጣን ላይ ያለው ሰው መሰሎቹን ይሰበስብና ሌሎቹን የሀገሩን ልጆች ይጨቁናል፡፡ መጀመሪያ የገዛ ወገኖቻቸውን ለዐረቦች በባርነት ሲሸጡ የነበሩት የሀገራቸው ሰዎች ነበሩ፡፡ አፍሪካውያን በባርነት ተሽጠው አሜሪካ ሲሄዱ ደግሞ ነጮቹ ጥቁሮቹን መጨቆን ጀመሩ፡፡ አየርላንዳውያን በእንግሊዞች መከራቸውን አይተዋል፡፡ ዓረቦች በዓረቦች ተሰቃይተዋል፡፡
አየሽ ቤተ መንግሥቱ ላይ ስትቀመጭ ሌላውን ለማግለል ሳጥን ትከፍቻለሽ፤ ከዚያ ሁሉንም በየሳጥኑ ታስቀምጭዋለሽ፡፡ የእምነት፣ የዘር፣ የመልክ፣ የአካባቢ፣ የቋንቋ ሳጥኖችን ከፍተው ሁሉንም እዚያ ስላስቀመጧቸው ተቀማጮቹ ሳጥኑን እንዳለ ተቀበሉት፡፡ ማንነታቸውም አደረጉትና ሳጥኑን ለማስቀረት ከመታገል ይልቅ ራሳቸውን ብቻ ከሳጥኑ ለማውጣት ይታገሉ ነበር፡፡ በሳጥኑ ዛሬ አህዮች ይገቡበታል፤ ነገ ፈረሶች፣ ከነገወዲያ ግመሎች፣ ከዚያም በጎች፣ ከዚያም ፍየሎች እየገቡበት ይቀጥላል፡፡ እኛም ዛሬ ያለሳጥን መኖር ከማንችልበት ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡ እኔን ሲያገኙኝ እንስሳ መሆኔን አይደለም የሚያዩት፤ የትኛው እንስሳ? ይላሉ፡፡ - ፈረስ፡፡ በዚህ አያቆሙም፡፡ ከዚያ ደግሞ የትኛው ፈረስ? የዱር ወይስ የቤት? ይቀጥላል፡፡ -የቤት፡፡ ለጭነት ወይስ ለግልቢያ? መቋጫ የለውም ልጄ፡፡ በትልቁ ሳጥን ውስጥ ራሳችን የሠራናቸው ትንንሽ ሳጥኖችም አሉ፡፡ በእነዚያም ውስጥ ሌሎች ትንንሽ ሳጥኖች አሉ፡፡››
‹‹ ለአንድ የገጠር ጉዞ በእኔ ላይ ይሄድ የነበረ አንድ ሰው ሲናገረው የሰማሁትን ታሪክ ልንገርሽ፡፡ ሰውዬው የከባድ መኪና ሾፌር ነበረ፡፡ ድሮ አሰብ እየተመላለሰ ዕቃ ይጭን ነበር፡፤ አንድ ጊዜ ወደ አሰብ ሲሄድ በረሃው ላይ መኪናው ይበላሽበታል፡፡ ከዚያም እዚያው ማደር ስለነበረበት ለምግቡ የሚሆን ፍየል ከአካባቢው የአፋር ሰው ይገዛል፡፡ አፋሩ ሰውዬው ፍየሏን መሸጥ ብቻ ሳይሆን አርዶ፣ ጠብሶ ያቀርብለታል፡፡ ሾፌሩ ምግቡን እየበላ የሸጠለትን የአፋር ሰው ‹‹እንግዲህ ትቼህ መብላቴ ነው፤ እንብላ እንዳልልህ የክርስቲያን ሥጋ አትበላም ብዬ ነው›› ይለዋል፡፡ አፋሩ ሰውዬ ይገርመውና ‹‹እኔው አዋልጄ፣ እኔው አሳድጌ፣ እኔው አርጄ፣ እኔው ጠብሼ ያመጣኋትን ፍየል ምንጊዜ ክርስቲያን አደረግካት?›› አለኝ ብሎ ሲያወራ ሰማሁት፡፡ አየሽ ሌላን ማግለል ስትፈልጊ የሆነ ነገር ትፈጥሪያለሽ፡፡ ማቅረብም ስትፈልጊ እንደዚያው፡፡››
‹ብዙ ዓይነት ነጻ አውጭዎች አሉ፡፡ እኔ አሁን የፈረስ ነጻ አውጭ ውስጥ ልግባ ወይስ የአህያ? ወይስ የበቅሎ?›› አለቻት ግልገሏ፡፡
‹‹የእንስሳት ነጻ አውጭ ካለ እዚያ ግቢ፡፡ አንቺ እንስሳ ነሽ፡፡ የቀረው ከመኖር የመጣ ስም ነው፡፡ እንስሳት ሁሉ ነጻ ሳይሆኑ በቅሎ ተለይታ ነጻ ልትሆን አትችልም፡፡ አንድን አካቢ ብቻውን ንጹሕ ማድረግ አትችይም፡፡ ምክንቱም ዝንቧ ከወዲያኛው ማዶ ትመጣለችና፡፡ ከእኛም ወገኖችኮ ሜዳ በመኖራቸው የተነሣ ‹የሜዳ ፈረስ›› ተብለው የቀሩ አሉ፡፡ እኛ ከሰው ተጠግተን ‹የቤት ፈረስ›› ለመሆን ቻልን፡፡ ‹‹የቤት አህዮች›› አሉ፡፡ ‹‹የሜዳ አህዮች›.ም አሉ፡፡ የስም ጉዳይ ነው፡፡ የአኗኗር ጉዳይ ነው፡፡ በቤተ መንግሥት ከነገሥታት ጋር የሚኖር አንበሳ ነበርኮ፡፡ የነገሥታቱ ዙፋን እንዲያውም የአንበሳ ቅርጽ ነበረው፡፡ በዚያው ዘመን ግን ንጉሡ ጫካ ወጥተው ሌላ አንበሳ ገድለው እየተዘፈነላቸው ይመጣሉ፡፡ ጀርባሽን ለመጋለብ ምቹ ካደረግሽው ምንጊዜም የተሻለ ተወዳጅ ትሆኛለሽ፡፡ እንግሊዞች ‹‹Better to ride on ass that carries me, than on a horse that throws me - የምትገለብጠኝን ፈረስ ከምጋልብ፣ የምትሸከመኝን አህያ ብጋልብ ይመረጣል›› ይላሉ፡፡
ቤት የቀረው ውሻ ዱር ከቀረው ውሻ ጋር በመለያየታቸው ዛሬ አንዱ አንዱን እንደ ጠላት ያባርረዋል፡፡ ሰው ብልጥ ነው፡፡ አንዱን ወደራሱ አቅርቦ ውሻ አደረገውና ‹‹ቦቢ›› እያለ በማቆላመጥ ነጻ የወጣ አስመሰለው፡፤ ሌላውን ደግሞ ቀበሮ፣ ተኩላ ብሎ ጫካ ተወውና እርሱን መግደል ጀግንነት እንዲሆን አደረገው፡፡ አሁን ውሾቹ የሠለጠኑና ነጻ የወጡ መስሏቸው ተኩላና ቀበሮ ሲያብርሩ ይኖራሉ፡፡ አየሽ ጉዳዩ የዘር አይደለም፡፡ በዘር ከሰው ተኩላ ለውሻ ይቀርበዋል፣ ቀበሮ ይዛመደዋል፡፡ ጉዳዩ የጥቅም ጉዳይ ነው፤ የመደብ ጉዳይ ነው፡፡ ከቀበሮውና ከተኩላው መካከል ደግሞ የተወሰነውን ይወስዱና ፓርክ ውስጥ አስገብተው ያለፈለት ያስመስሉታል፡፡ እርሱም ማግኘት የሚገባውን ሳይሆን ራሱን ከጫካው ኑሮ ጋር ስለሚያነጻጽር ‹ተመስገን› እያለ ይኖራል፡፡››
‹‹ነጻነት የፍጡር ሀብት ነው፡፡ ለእነ እገሌ ተብሎ የሚቆረስ አይደለም፡፡ ጨቋኙም ተጨቋኙም ነጻ ካልወጣ ሙሉ ነጻነት አይገኝም፡፡ ጨቋኝነት ከአስተሳሰብ ባርነት የሚመጣ ነው፡፡ ከአመለካከት ድህነት የሚከሰት ነው፡፡ ሙሉ ነጻነትን ለማግኘት እርሱን ነጻ ማውጣት አለብሽ፡፡ ካልሆነ ግን ጉዞው አንዱን ጨቋኝ በሌላ ጨቋኝ መተካት ነው የሚሆነው፡፡ አፍሪካውያንኮ ራሳቸውን ከአውሮፓውያን ነጻ ማውጣት አላቃታቸውም፡፡ ያቃታቸው ራሳቸውን ከራሳቸው ነጻ ማውጣት ነው፡፡ ነጭ ጨቋኞች በጥቁር ጨቋኞች ተተኩ፡፡ ቅድም እንዳልኩሽ ሳጥኑን ካላጠፋሽው ታግሎ ከሳጥኑ የወጣው ሁሉ በፋንታው የተሸነፈውን እርሱ ወደወጣበት  ሳጥን መክተቱ የማይቀር ነው፡፡
‹‹ደግሞስ ለምን በማትቀይሪው ነገር ጊዜሽን ታጠፊያለሽ? አሁን አንቺ በቅሎ ሆነሻል፡፡ አለቀ፡፡ ከእንግዲህ አህያ፣ ፈረስ፣ አንበሳ፣ ጅብ ፣ ድመት ልትሆኝ አትችይ? መሆን ለምትፈልጊው ነው መታገል ያለብሽ? በእጅሽ ላይ ላሉት ዕድሎች ነው መታገል ያለብሽ፤ ልትለውጫቸው ለምትችያቸው ዕድሎች ነው መታገል ያለብሽ፤ ልታሸንፊያቸው ከምትችያቸው ነገሮች ጋር ነው መታገል ያለብሽ፡፡ ትናንትን በነገ ለመቀየር ታገዪ፤ ትናንት ውስጥ ገብተሸ ግን እቀይረዋለሁ አትበዪ፤ መጀመሪያ አንቺ ራስሽ ከትናንቱ ውጭ፤ ያ ያለፈ ነገር ነው፡፡ ታሪክ አይታረምም፤ ሆኗልና፡፡ በታሪክ ውስጥ የተፈጠረ ችግር ግን በቀጣይ ታሪክ ይታረማል፡፡ ምን ሆነ? የሚለው አይለወጥም፤ ምን ይሁን? የሚለውን መለወጥ ግን ይቻላል፡፡ ዛሬ ላይ ሆነሽ የመጣሽበትን ማስተካከል አትችይም፤ የሚትሄጅበትን ግን ትችያለሽ፡፡ ብዙዎቹ ነጻ አውጭዎች ትናንትን ነጻ ለማውጣት የተቋቋሙ ናቸው፡፡ አንቺ መግባት ያለብሽ ነገን ነጻ ሊያወጣ የተቋቋመ አካል ከተፈጠረ ብቻ ነው፡፡
‹‹አፍሪካውያን ‹‹until the lions have their own historians tales of hunt will always glorify the hunters- አንበሶች የራሳቸው ታሪክ ጸሐፊዎች እስኪኖሯቸው ድረስ ስለ አደን የሚጻፈው ታሪክ ሁሉ ምጊዜም አዳኞችን የሚያገንና የሚያከብር ይሆናል›› ይላሉ፡፡ ዛሬ ከአንድ ወገን ብቻ እየሰማን የምንፈርዳቸው ፍርዶች በታሪክ ተሠሩ ከምንላቸው ስሕተቶች በላይ እንድንሳሳት የሚያደርጉን ናቸው፡፡ የማናውቃቸውና ያልሰማናቸው፤ ምናልባትም ወደፊትም ልንሰማቸው የማንችላቸው ታሪኮችም አሉን፡፡ ትናንት ያለፈ በመሆኑ ለፍርድ እጅግ አስቸጋሪ ነው፡፡ ሰሎሞን ዴሬሳ የተባለ ሰው ‹አንተ ዘርህ ምንድን ነው?› ሲባል ‹‹በቅድመ አያቴ ደጅ ማን እንዳለፈ እኔ ምን ዐውቃለሁ›› ይል ነበር፡፡ በአንቺስ ቅድመ አያት በር ማን እንዳለፈ ምን ታውቂያለሽ? መጠኑና ዘመኑ ይለያያል እንጂ ‹ሌላ› የሚለውን አካል ሳይገድል፣ ሳያጠፋ፣ ሳይጨቁን፣ ሳይቀማ እዚህ የደረሰ የለም፡፡ ግን ታሪክ እንደተራኪው ነው፡፡
‹‹ሁላችንንም መከራውና ግፉ፣ ጭቆናውና የደረሰብን ነገር ሁሉ አስተባብሮናል፡፡ በየዘመናቱ ቤተ መንግሥቱን የተጠጋ ተሸልሟል፡፡ አምሮበታል፡፡ ሌላውን ለማስገበርም ዘምቷል፡፡ እኛ አህዮች፣ ፈረሶችና በቅሎዎች ነንኮ ሌሎች እንስሳት እንዲታደኑ አብረን ከሰዎች ጋር የዘመትነው፡፡ በእኛ ዘምተው ሌላ ሀገር የሚገኙ ፈረሶችንና አህዮችን እንዲዘርፉ አድርገናልኮ፡፡ ከዘመቻው በኋላ ለእኛ የተሻለ ነገር ጣል ሲደረግልን እነርሱ ግን በባዶ ሜዳ አድረዋልኮ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ለእኛ እነርሱ ይቀርቡን ነበር፡፡ ነገር ግን ቤተ መንግሥቱን ስትጠጊ እንዲህ አታስቢም፡፡ በታሪካችን ውስጥ የደረሱብንንና ያደረስናቸውን ብንቆጥራቸው ከምንለያይበት የምንመሳሰልበት ይበልጣል፡፡ ግን ምን ያደርጋል ከሳጥኑ ወጥቶ የሚያስብ የለም፡፡ ሳጥኑ ውስጥ ስትሆኚ ደግሞ ያንቺ ብቻ ነው የሚታይሽ፡፡
‹‹መቼም በእንስሳት ታሪክ ቀደምት ከሚባሉት አንደኛዎቹ ቲቤታውያን ናቸው፡፡ እንዲህ ይላሉ ‹‹አንጥረኛው ጥበበኛ ከሆነ ብረትና ነሐስ ሊዋሐዱ ይችላሉ››፡፡ አሁንም እኛ አንድ ልንሆን ያልቻልነው አንድ የሚያደረግን ነገር ስለሌለ ሳይሆን አንድ የሚያደርገን ጥበበኛ አንጥረኛ ስለሌለ ነው፡፡ እስኪ ተመልከቺው፤ ቤተ መንግሥት የኖረውን አንበሳኮ ነው ‹‹አንበሳ ሲያረጅ የዝንብ መጨዋቻ ይሆናል›› የሚሉት፡፡ ታድያ ከጫካው አንበሳ ምን የተለየ ነገር አገኘ? የቤት አህያም ሆነ የጫካ አህያ ሲያረጁ ሁለቱንም አውሬ ይበላቸዋል፡፡ ቤት ውስጥ የኖረውም ውሻ ሲያረጅ ዞር ብሎ የሚየው የለም፡፡ ስለዚህ ልጄ አሁን የሚያስፈልገን የእገሌ ነጻ አውጭ ድርጅት ሳይሆን ‹የአስተሳሰብ ነጻ አውጭ ድርጅት›› ነው፡፡ አስተሳሰብሽ ነጻ ሲወጣ ‹‹መጀመሪያ እኔ እንስሳ ነኝ ወይስ በቅሎ?›› የሚለውን ጥያቄ ራስሽ ትመልሽዋለሽ፡፡

Oct 29, 2012

በታሪክ መርካት


በታሪክ መርካት

click here for pdf
(ፎቶ -በአሜሪካ የኢትዮጵያ  ኢምባሲ ድረ ገጽ)
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ31 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ የመመለሱ ፌሽታ ሕዝቡን አልለቀቀውም፡፡ ተጨዋቾቹና ፌዴሬሽኑም በዚሁ ደስታ ውስጥ ናቸው፡፡ ስለ እሑዱ ድል እንጂ ስለ ቀጣዩ ውድድር የሚያስብ ግን ያለ አይመስልም፡፡ ሌሎቹ ቡድኖች እስከ ጥር ወር ድረስ ምን እንደሚሠሩ በሚናገሩበት ጊዜ እንኳን የኛው ቡድን እስከ ጥር ወር ድረስ ምን እየሠራ እንደሚቆይ አይታወቅም፡፡
እንዴውም እንደምንሰማው ከሆነ አንዳንድ ተጫዋቾቻችን በየመጠጥ ቤቱ እየተጋበዙ በሸክም ሆኗል አሉ የሚወጡት፡፡ ምነው ሲባሉ ‹ድል አድርገናልኮ› ነው መልሱ፡፡
ይኼ በትናንት ድል እየረኩ ነገን የመርሳት አባዜ የቆየ በሽታችን ነው፡፡ በአድዋ ጦርነት ጣልያንን ወኔያችንን ተጠቅመን፣ ጀግንነታችንን ተኩሰን ፈጣሪም ረድቶን ድል አደረግናት፡፡ በጥቁር አፍሪካ ምድር ቅኝ ገዥዎችን ድል ያደረገ ጥቁር ሕዝብ መሆናችንን አስመሰከርን፡፡ ታሪክ ሠርተን ታሪክ አየን፡፡

ጣልያንን የአድዋው ውርደቷ ሲቆጫት ነው የኖረው፤ ያንን ውርደቷን እንዴት እንደምታራግፈው ስትመክር፣ ስትሠራና ስትፈጥር ኖረች፡፡ እኛ ደግሞ የአድዋን ድል ስናከብር፣ በድሉ ፌሽታ ስንጥለቀለቅ ከረምን፡፡ እኛ ዐርባ ዓመት ስለ አድዋ ስንዘፍን፣ እነርሱ ዐርባ ዓመት ውርደታቸውን ለማራገፍ ሲሠሩ ከረምን፡፡ ለኛ ጣልያንን ተወግዞ እንደወጣ ሰይጣን ተመልሳ የማትመጣ አድርገን ቆጠርናት፡፡

ከዐርባ ዓመት በኋላ በ1928 ዓም ጣልያን ካለፈው ስሕተቷ ተምራ አውሮፕላንና መርዝ ሠርታ፣ ዘመናዊ ወታደር ትጥቅ አሟልታ፣ እስከ አፍንጫዋም ታጥቃ መጣች፡፡ እኛ ግን እነዚያኑ አድዋ የወሰድናቸውን መሣርያዎችና አጋሠሶች ይዘን ማይጨው ዘመትን፡፡ እናም በማይጨው የሆንነውን እናውቀዋለን፡፡
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ረሃብ፣ ወረርሽኝና ተስቦ እየደጋገመ ሀገሪቱን ሲመታና ሲያደቅቅ እናገኛለን፡፡ እያንዳንዱን የመከራ ጊዜ በጸሎትም፣ በእሳትም፣ በሞትም ስናሸንፈው ሌላ መከራ የማይመጣ ይመስል ያኛውንና ያለፈውን እንዴት እንደተወጣነው ብቻ በመተረክና በመዝፈን ጊዜውን እንጨርሰዋለን፡፡ ያም የመከራ ዘመን ጊዜውን ጠብቆ እንደገና ይመጣል፡፡
ጅርመኖች በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሀገራቸው እንዳልነበረች መሆንዋ፣ ከናዚ አስተሳሰብ ጋር በተያያዘ ስሟ መጥፋቱ፣ ጀርመናዊ ነኝ ማለት እስኪያሳፍር ድረስ መድረሱ አስቆጭቷቸው ለአርባ ዓመታት ሠሩ፡፡ በዐርባ ዓመት ጊዜ ውስጥ ጀርመን የዓለምን አራተኛ ኢኮኖሚ የምታስተዳድር ሀገር ሆና ወጣች፡፡ እኛ ግን የአፍሪካን ዋንጫ እንኳን ለመሳተፍ 31 ዓመታት ፈጀብን፤ ለምን? ቢባል በታክ የሚዝናና እንጂ በቁጭት የሚሠራ ስላላገኘን፡፡
አሁንም በእግር ኳስ ቡድኑ ላይ የምናየው ይኼንኑ ነው፡፡ ትናንት አሸነፍን፤ መልካም፡፡ ነገር ግን የኛ ደስታ እንደ ሄሊኮሜት በዘመናት አንድ ጊዜ ብቻ ነው እንዴ መምጣት ያለበት? ያለፈ ድል ለቀጣዩ መነሻ ይሆናል እንጂ ስንቅ ይሆናል እንዴ? አሁን መጠየቅ ያለብን ከነማን ጋር ደረሰን? የሚለውኮ አልነበረም፡፡ አሠልጣኝ ሰውነት እንዳሉት ‹ከማንም ጋር ይድረሰን፣ ከተዘጋጀንና ከሠራን እናሸንፋለን፤› ካልሠራን ግን ከራሳችንም ጋር ተጫውተን አናሸንፍም፡፡
ለምን እንረሳለን፤ እኛኮ በአፍሪካ ዋንጫ ከሁሉም ቡድኖች የበለጡ ጎሎችን ያስተናገድን ነን፤ በአፍሪካ ዋንጫ ከሚሳተፉ ቡድኖች በፊፋ ደረጃ ዝቅተኛ ደረጃ ካላቸው መካከል የምንመደብ ነን፤ ሌሎቹኮ ተጨዋቾቻቸውን  ከአውሮፓ እየጠሩ ነው፣ አራትና አምስት የወዳጅነት ጨዋታ ከአውሮፓ ቡድኖች ጋር ለማድረግ ዕቅዳቸውን ይፋ አድርገዋልኮ፡፡
     ሦስተኛውን የአፍሪካ ዋናጫ ያሸነፈው ቡድን 
           ( ፎቶ -ከሪፖርትር)
እኛ ሱዳንን ስላሸነፍን ተዘጋጅቶ የሚጠብቀን እንጂ ፈርቶን የሚሸሽኮ የለም፡፡ እንዴት አሸነፉ? ምን ዓይነት ስልት አላቸው? ጠንካራና ደካማ ጎናቸው ምንድን ነው? እያለ ተንትኖ የሚጠብቀን እንጂ አርድ አንቀጥቅጥ የለበስን ይመስል ማንም አይደነግጥልንም፤ ያለፈው ድላችን ተጋጣሚዎቻችንን ይበልጥ ተዘጋጅተው እንዲጠብቁን ያደርጋቸዋል እንጂ ‹እንደ ሰም አቅልጦ፣ እንደ ገል ቀጥቅጦ› አይጥላቸውም፡፡
ባለፉት 31 ዓመታት የዛሬ ሠላሳ አንድ ዓመት ማን በጭንቅላት በገጫት ኳስ ለአፍሪካ ዋንጫ እንዳለፍን ስንተርክ ሰነበትን፡፡ ለመሆኑ ቀጣዩን የአፍሪካ ዋንጫስ? ‹ሳላዲን ሰይድና አዳነ ግርማ እንዲህና እንዲያ አድርገው ባገቡት ግብ ነበር ያለፍነው› እያልን ለምን ያህል ዓመት ይሆን የምንተርከው?
ይህ ሀገሩ ከፍ ስትል የሚወድ ሕዝብ ደስታው ምንያህል እንደነበረኮ አይተነዋል? ኢትዮጵያ ቡድን እንጂ ሕዝብ አላጣችም፤ ፌዴሬሽን እንጂ ሕዝብ አላጣችም፡፡ ይልቅስ አሁን መነጋገር ያለብን ይህንን ደስታ እንዴት ዘላቂ ማድረግ እንደምንችል ነው፤ እንዴት ነው የአፍሪካ ዋንጫ ብርቅ የምይሆንብን ደረጃ የምንደርሰው? እንዴት ነው የዓለም ዋንጫን በቴሌቭዥን ብቻ ከማየት የምንላቀቀው? እንዴት ነው በጠንካራ መሠረት ላይ የተመሠረተ እግር ኳስ የምናደራጀው? እንዴት ነው የባለሃብቶችን ድጋፍ ከሽልማት ወደ ቀድሞ መደገፍ የምንቀይረው?
ብዙ ሥራ አለብን፡፡ ደስታው ይብቃ፤ ፌሽታውም ልክ ይኑረው፤ እርሱ የኛ ሆኗልና ማንም አይነጥቅብንም፤ አሁን የኛ ስላልሆነው የአፍሪካ ዋንጫ እናስብ፡፡ ታሪክ ላይ መተኛት ብዙ ጊዜ ጎድቶናልና ይብቃን፡፡

Sep 3, 2012

የተማርንበትም የተማረርንበትም ሰሞን ( ዳንኤል ክብረት)

የተማርንበትም የተማረርንበትም ሰሞን



(ፎቶው የቢቢሲ ነው)
የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ከተረዳበት ሰዓት ጀምሮ ሀገራችን አዲስ መልክ ይዛለች፡፡ ያለፉት ቀናት ስለራሳችን የተማርንባቸው፤ በራሳችንም የተማረርንባቸው ቀናት ነበሩ፡፡ እስኪ ከተማርንባቸው ልጀምር፡፡
ትዝ ይለኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ከውጭ ሀገር ወደ አዲስ አበባ የሚገቡበት ጊዜ ነበር፡፡ በቦሌ ጎዳና ፖሊሶች አዚህም እዚያም በዛ ብለዋል፡፡ እኔ ደግሞ አልሰማሁም ነበርና እዚያ አካባቢ ለሥራ መሄድ፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ መንገዱ ጭር አለ፡፡ ፖሊሶችም መጡና ከአካባቢው ዘወር እንድንል ነገሩን፡፡ የሚገርመው ነገር ግን አካባቢው በአፓርታማዎች የተጠቀጠቀ ነበርና ዘወር የምንልበት ቦታ ጠፋን፡፡ ፖሊሱ ግን አሁንም አሁንም ከአካባቢው ዘወር እንል ዘንድ ያዝዛል፡፡ ግን የት ዘወር እንበል? በመጨረሻ መጣና በአፓርታማው የታችኛው ክፍል ካሉት ቤቶች አንዱን አንኳኳ፡፡ አንዲት በእድሜ ጠና ያሉ ሴት ከፈቱ፡፡ ‹‹ግቡ›› አለን ፖሊሱ፡፡ አንድ ሰባት እንሆናለን፡፡ ግራ ገብቶን ተያየን፡፡ ከጀርባችን ገፋ ገፋ እያደረገ ሰው ቤት ውስጥ አስገባን፡፡ ስለ ቻይና ባቡርና ፖሊስ ያየሁት ፊልም ነው ትዝ ያለኝ፡፡ ሴትዮዋ በሩን እንዲዘጉ ተነገራቸው፡፡ ተዘጋ፡፡
አሁንም ሰው ቤት ገብተን ተያየን፡፡ ደግነቱ ሴትዮዋ ተግባቢ ናቸውና ‹‹በሉ እንግዲህ መንግሥት ካዛመደን ዐረፍ በሉና ሻሂ ጠጡ›› አሉን፡፡ እኛም ሳቅ እያልን ባገኘነው ወንበር ተቀመጥን፡፡ እዚያ ተቀምጠንም በባለ ሥልጣኖቻችንና በሕዝባቸው መካከል ስላለው ግንኙነት ተቸን፤ አማን፤ ሃሳብም ሰነዘርን፡፡ ከዚህ በፊት ያጋጠመንንም ተጨዋወትን፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስከሬን በመጣበት ማታ ይህንን አጋጣሚ ነበር የማስበው፡፡ ሕዝቡ ግልብጥ ብሎ መንገድ ላይ ወጥቶ ነበር፡፡ በአንዳንድ አደረጃጀቶች በኩል ከመጡ ጥቂት ሰዎች በቀር አብዛኛው ሰው በራሱ ፈቃድ ኀዘኑን ለመግለጥ ታሪክም ለማየት ነበር የወጣው፡፡ ጧፍ እንኳን ያበራው ዕለቱ የፍልሰታ ጾም ማብቂያ የኪዳነ ምሕረት ዋዜማ በመሆኑ በቦሌ መድኃኔዓለም፤ በኡራኤል፣ በእስጢፋኖስና በግቢ ገብርኤል አካባቢ ለበዓሉ ጧፍ ለመሸጥ ከተቀመጡት እናቶች እየገዛ ነበር፡፡ ጧፍ ማብራትን ሕዝቡ ራሱ ያመጣው የአቀባበል ሥርዓት ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ግን በየ ቀበሌው ተዳረሰ፡፡
ያን ምሽት ሕዝቡ ወደ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላምና ያለ አንዳች ችግር ሲገባ ነበር፡፡ ከፖሊስ ጋር ግርግር የፈጠረ አልነበረም፡፡ ጨዋነት ጎልታ የወጣችበት ምሽት ነበር፡፡ በመንገድም ላይ ቢሆን የነበረው ሁኔታ አስቀድሞ ያልተገመተው የሕዝቡ ማዕበል ከተጠበቀው በላይ መሆኑ ነበር፡፡ የጸጥታ አስከባሪዎች መጀመርያ ላይ አስከሬኑ ከሕዝብ ርቆ ግራና ቀኝም ተከልሎ እንዲያልፍ አስበው ነበር፡፡ ሕዝቡ ግን ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ እያለቀሰና እየተከዘ አብሮ መጓዝን መረጠ፡፡ ነገሩንም ሲረዱት እነርሱም ተውት፡፡ እንዲያ ዝናብ እየቀጠቀጠው፤ እንዲያ ብርድ እያንቀጠቀጠው የዐሥር ደቂቃ መንገድ አራት ሰዓት እስኪፈጅ ድረስ አስከሬኑን በክብር አጅቦ፤ ራሱ ባወጣው ሥርዓትና አሠራር ተጓዘ፡፡ ምንም ዓይነት የጸጥታ ችግር ሳይፈጠር አስከሬኑ ቤተ መንግሥት ደረሰ፡፡
ለመሆኑ ከዚህ መማር የለብንም?
የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋ ሕዝብ ነው ስንል ምን ማለታችን ነው?
ይህ ሕዝብ መሪዎች ወይም ባለ ሥልጣናት ባለፉ ባገደሙ ቁጥር ሊንገላታ የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ሊከበር እንጂ ሊሰጋ የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ቀርበው ሊያወያዩት፤ ችግሩን በቅርብ ሊያዩለት የሚገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ወደ ሀገሪቱ ከሚመጡ እንግዶች በላይ ሊከበር የሚገባው ሕዝብ ነው ማለታችን ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝቶ ዘመዱን ለመቀበል አትገባም ውጭ ቆመህ ዝናብ ይቀጥቅጥህ ሊባል የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ፍትሕ ለማግኘት ዓመት ሁለት ዓመት ሊጉላላ የማይገባው ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ በጎ ለሚሠሩ ሁሉ ስሕተታቸውንና ጥፋታቸውን እያወቀ እንኳን የሚደግፍ ነውና ሊያሳዝኑትና ሊያቀስቀይሙት የማይገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ ይህ ሕዝብ ኮንደሚንየም ብርቅ ሊሆንበት የመይገባ ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ለመጀመርያ ጊዜ በሕዝብ ታጅበው ቤተ መንግሥት ሲገቡ አየሁ፡፡ ምናለ በሕይወት በነበሩ ጊዜ ይህ ሆኖ በነበረ፡፡ ይኼው ሕዝብ ነውኮ ያኔም የነበረው፤ ይኼው ጨዋ ሕዝብ እኮ ነው የሚያጅባቸው፤ ይኼው ጨዋ ሕዝብ እኮ ነው የሚጠይቃቸው፤ የሚያወያያቸው፡፡ ይህ ሕዝብኮ እዚሁ የነበረ ነው፡፡ ከአውሮፓ ወይም ከእስያ አልመጣም፡፡ ቀጣዮቹም ባለሥልጣናት ይህንን ትምህርት መውሰድ አለባቸው፡፡ ባለ ሥልጣናት ሆይ ሰው ሁኑ፡፡ ሰው ያልሆነው አምላክ እንኳን ሰው ሆኖ በሰው ቋንቋ ተነጋግሯል፡፡ ከሰው ጋር ውሎ አድሯል፤ ከሰው ጋር በልቷል፡፡ ከሰው ጋር ተጉዟል፡፡ እናንተ ታድያ ሰው ብትሆኑና ከሰው ጋር ብትኖሩ ምናለበት? እርሱ አምላካችን ሰው ሆኖ የሰውን መከራ፣ ስቃይና ኀዘን ቀምሶታል፡፡ እናንተስ ሰው ሆናችሁ መከራችንን፣ ችግራችንንና ኀዘናችንን ብትቀምሱት ምናለ? እስከ መቼ በሪፖርትና በስብሰባ ብቻ እንገናኛለን? እስከ መቼ በቴሌቭዥን ብቻ እንተያያለን?
ሪፖርት ቢጽፉት እንደ አካል አይሆንም
ቴሌቭዥን ቢያዩት እንደ አካል አይሆንም
ስብሰባ ቢጠሩት እንደ አካል አይሆንም
እንገናኝና ልናገር ሁሉንም
ተብሎ መዘፈኑን አልሰማችሁም?
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ቤተ መንግሥት ተከፈተ፡፡ ይህ ደግሞ አቶ መለስ የሠሩት ሌላው ታሪክ ነው፡፡ እኔ ስለዚህ ቤተ መንግሥት ክፉ እንጂ ደግ ሰምቼ አላውቅም ነበር፡፡ በተለይ በደርግ ዘመን ስለነበረው ሁኔታ የተጻፉት ሁሉ ስለዚያ ቤተ መንግሥት የሆረር ፊልም ያህል ሲያስፈራሩን ነበር፡፡ ምናልባት ሕዝብ በብዛት ሆኖ ወደዚያ ቤተ መንግሥት የገባው በንጉሡ ጊዜ ግብር ለመብላት ሳይሆን አይቀርም፡፡ እርሱንም ሰምተን እንጂ አላየንም፡፡ ከዚያ ወዲያ ባለፉት ዓርባ ዓመታት ለሕዝብ የተከለከለ ቦታ ነበር፡፡ እንዴው አልፎ አልፎ ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ካልኖረ በቀር ቤተ መንግሥቱና ሕዝቡ በማኅበራዊ ነገር አልተገናኝተውም ነበር፡፡
(ፎቶው የቢቢሲ ነው)
እነሆ ሕዝብ ተሰለፈና ቤተ መንግሥት ገባ፡፡ ይህንንም ቢሆን ሕዝብ የፈጠረው ይመስለኛል፡፡ የአቶ መለስ ሞት ከተረዳበት ሰዓት ጀምሮ ሚዲያዎቹን ያጨናነቀው ጥያቄ የት ሄደን ልቅሶ እንድረስ? የሚለው ነበር፡፡ የቀብር አስፈጻሚው ብሔራዊ ኮሚቴም ለዚህ በጎ ምላሽ በመስጠቱ ይመሰገናል፡፡ ወደ ቤተ መንግሥት እንደሚገባ በቀበሌም በአደረጃጀትም፣ በሚዲያም ከመነገሩ በፊት ነበር ሕዝብ ቤተ መንግሥቱን ያጥለቀለቀው፡፡ [እዚህም ላይ ሌላ አስመራሪ ነገር ገጥሞን ነበር፡፡ በሀገር ውስጥ ያሉት የመንግሥት ሚዲያዎች ሰው ግልብጥ ብሎ የወጣው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ፖሊሲና ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ በመቀበሉና በመጠቀሙ ነው ይሉ ነበር፡፡ የውጮቹ ደግሞ ተገድዶና ተደልሎ ነው፤ አደርባይ ስለሆነም ነው ይላሉ፡፡ የሁለቱም ችግር ሕዝብን ካለ ማወቅና ለራሱ ጥቅም ሁሉንም ነገር ከመጎተት የመጣ ነው፡፡
አስከሬኑ አዲስ አበባ ሲገባም ሆነ በቤተ መንግሥቱና በየአካባቢው በተከናወነው ልቅሶ ሕዝቡ በፖሊሲዎችና በስትራቴጂዎች ሙሉ በሙሉ ተስማምቶ ብቻ የወጣ አይደለም፡፡ ምክንያቱ ልዩ ልዩ ነው፡፡ በርዕዮተ ዓለማቸውና በሥራቸው ተደስቶ ነገር ግን በሆነው ነገር አዝኖ የወጣ አለ፡፡ በአንዳንድ ሃሳባቸው ተስማምቶ በሌላው ተለያይቶ በመሞታቸው ግን አዝኖ የወጣ አለ፡፡ በእርሳቸው አስተሳሰብም ሆነ ሥራ ምንም ሳይስማማ፣ ነገር ግን የሀገሩ መሪ በመሞታቸው አዝኖ የወጣም አለ፡፡ ታሪክ ለማየት ሲልም የወጣም አለ፡፡ እርሳቸውን እየተቃወመም በባሕሉ ልቅሶ መድረስ አለብኝ ብሎ የወጣም አለ፡፡ ይህ ሁሉ እኛን ይደግፋል ብሎ ማሰብና በዚህ ተመሥርቶ ውሳኔ መወሰን ከስሕተት ይጥላል፡፡
ይህ ሕዝብ ተገድዶ የወጣ አድር ባይ ነው ብሎ ማሰብም ሌላው ስሕተት ነው፡፡ ምናልባት እንዲያውም አብዛኛው ኀዘኑን በባህሉ መሠረት ለመግለጥ የወጣ ነው፡፡ ጥቂት ሊገደዱ የሚችሉ ይኖራሉ፤ ታይተዋልም፡፡ ውጡ ብለው መመርያ ለማውጣት የሞከሩ ታናናሽ ባለ ሥልጣናትም ነበሩ፡፡ ሕዝቡ ግን የተጓዘው በራሱ ነው፡፡ መቼም ሕዝብን በግድ ማሰለፍና አደባባይ ማውጣት ይቻል ይሆናል እንጂ እንዲያለቅስ፣ እንዲደነግጥ፣ ፌንት እንዲያደርግ፤ መሬት እንዲንከባለል ማድረግ የሚቻል አይመስለኝም፡፡ በርግጥ ለደረት ድቂያ፣ ለአስለቀሽና ለእድር ድንኳን አንዳንድ ቅመማ ቅመም ሳይጨመርበት አይቀርም፡፡ ሁሉንም በአንድ ፋይል ጠቅልሎ ተታልሎ ነው፣ ተገድዶ ነው፣ አድር ባይ ሆኖ ነው ማለት ግን የኢትዮጵያን ሕዝብ አለመረዳትን የሚያሳብቅና ወደ ተሳሳተ ውሳኔም የሚያደርስ ነው፡፡]
ሕዝቡ ባህላዊ ሕዝብ ነው፡፡ አዛኝ ሕዝብም ነው፡፡ ያዘነበት የየራሱ ምክንያት አለው፡፡ አንድ ያደረገው ማዘኑ ነው፡፡ ራሳቸውን የሚስቱ፤ የሚያደርጉትን የማያውቁ፤ እየሆነ ያለውን ነገር መቀበል ያቃታቸው፤ የነገሮች መገጣ ጠም ያስደነገጣቸው፤ መሪ ሲሞት፤ ሲለቀስለትም አይተው ባለማወቃቸው ግራ የገባቸው ሰዎች ነበሩ፡፡ ሁሉም ግን አዝነው ነበር፡፡ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ ዐዋቂዎች፣ አረጋውያን፤ የተማሩ፣ የከተማ የገጠር ሁሉም ወደ አራት ሰዓታት የፈጀ ሰልፍ ይዘው ኀዘናቸውን ለመግለጥ ገብተዋል፡፡[እዚህ ላይ ግን ሌላ የሚያስመርር ነገር ነበር፡፡ ሕዝብ አዝኗል፡፡ ኀዘኑን የሚገልጥበት ቦታም ይፈልጋል፡፡ በባሕላችን ኀዘናችንን የምንገልጥበት ቦታ እንፈልጋለን፤ እገሌ ሞተ ሲባል ልቅሶ የሚደረሰው የት ነው? መባሉ የተለመደ ነው፡፡ አንዳንድ እወደድ ባዮች ግን ልቅሶውንና ወደ ቤተ መንግሥት መሄዱን እንደ ግዴታ ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ ለምን? ይህ ከማማረር በቀር ምን ፋይዳ ይሰጣል? ወይስ እኛ ያልሠራነው ሥራ እንደ ተሠራ አይቆጠርም? በመጨረሻዎቹ ሦስት ቀናት በተደረገው የስንብት መርሐ ግብር ጊዜ በየአካባቢው የታየው አስገዳጅ የመሰለ ቅስቀሳ የሕዝቡን ስሜት ወደ መረበሽ ተሻግሮ ነበር፡፡ ፈጽሞ መደገም የሌለበት አስመራሪ አሠራር አንዱ ይኼ ነው፡፡]
ምንም እንኳን የሕዝቡ ቁጥር ከተጠበቀው በላይ ቢሆንም፤ ምንም ያህል ያልታሰበ ቢሆን ሕዝቡን ለማስተናገድና ሕዝቡም እንዳይቸገር ለማድረግ የጸጥታ አስከባሪዎች ያደርጉት የነበረው ጥረት ሊደነቅ ይገባዋል፡፡ የማመናጨቅ፤ የመሳደብ፤ የመገፍተር፣ አይቻልም አይቻልም ብሎ የመዝጋት ጠባይ አይታይም ነበር፡፡ መጀመርያ በአንድ በር ፤ በኋላም በሁለት በር፤ ከዚያም በዋናው በር በኩል በማስገባት በመስተንግዶ ሠልጥነዋል ከሚባሉት ከሆቴል አስተናጋጆች እንኳን በማይገኝ ትኅትናና ቅልጥፍና ለማስተናገድ ጥረዋል፡፡
እኔ ይህንንም ነገር ነው እንማርበትና እንቀጥል የምለው፡፡ ድሮ ድሮ ሌባና ፖሊስ ስንጫወት ፖሊስ አባራሪ ሌባ ተባራሪ ይሆን ነበር፡፡ ይህ ጨዋታ ሌባ በሌለበትም ሳይቀጥል አልቀረም፡፡ ሕዝብና ፖሊስ ተከባብሮ እንጂ ተፈራርቶ መኖር የለበትም፡፡ ፖሊስ ሕዝቡን የሚያገለግል፤ ለሕዝቡም ጸጥታ የሚተጋ መሆኑን ማስመስከር አለበት፡፡ ፖሊስን ወንጀለኛ ብቻ እንዲፈራው መደረግ አለበት፡፡ ‹‹ፖሊስ እጠራብሃለሁ›› እያሉ ልጆችን ማስፈራራት እንዲቀር ፖሊሶቹ ራሳቸው መሥራት አለባቸው፡፡
ይህ የአሁኑ ትውልድ ቤተ መንግሥት ምን እንደሚመስል፤ የሚመራው ሰው የት እንደሚሠራ፤ የት እንደሚኖር ለመጀመርያ ጊዜ ያየበት ዕድል ነው የገጠመው፡፡ እንዲያውም አንዳንዶች የጠቅላይ ሚኒስትሩን ቢሮና ቤት አይተው ተገርመዋል፡፡ እንደዚያ እንደማይመስላቸው ይናገሩ ነበር፡፡ ካሰቡት በታች ሆኖባቸው ‹‹እኒህ ሰው እዚህ ነበር እንዴ የሚኖሩት?›› ብለዋል፡፡ ለምን ግን የራሳችንን ቤተ መንግሥት በሕልም ብቻ እንድናየው ተደረገ? ለምንድን ነው ስለ መሪዎቻችን ብዙ ነገር እንዳናውቅ የሚደረገው? ብናውቅ ምን ይሆናል? ያኔስ ቢሆን አሁን ያወቅነውን አልነበር የምናውቀው? ምን የተለየ ነገር ነበረው?
ስለ አቶ መለስ ጠባያት፣ የሥራ ሁኔታ፤ ትጋትና ማንነት በሕይወታቸው እያሉ ከምናውቀው በላይ አሁን ነው የሰማነው፡፡ መስማታችን እሰየው፡፡ ግን ይህንን ቀደም ብሎ መስማት አይቻልም ነበር? በርግጥ እርሳቸው ስለ ራሳቸው መናገርም ሲነገር መስማትም ብዙም አይፈልጉም ነበር ይባላል፡፡ የርሳቸው አለመፈለግ መልካም፡፡ ግንኮ መሪ የሚፈልገውን ብቻ አይሠራም፤ ሕዝብ የሚያስፈልገውንም ጭምር እንጂ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ማለት ግለሰብነት ብቻ አይደለም፡፡ ሕዝባዊ አካልም ነው፡፡ ሕዝብ ስለ መሪው ማወቅ አለበት፡፡ ሊነገረው ይገባል፡፡ ስለ መሪው የማያውቅ ሕዝብ ሁለት ነገር ይገጥመዋል፡፡ ወይ ባለ ማወቅ መሪውን ይቃወመዋል፤ ወይም ባለ ማወቅ መሪውን ይደግፈዋል፡፡ ሁለቱም ግን አደገኞች ናቸው፡፡ ባለማወቅ የደገፈም ሲያውቅ ይሸሻል፤ ባለማወቅ የተቃወመም ሲያወቅ ይፀፀታል፡፡
ከሁሉም በላይ የተደነቅኩት ግን በቀብሩ ዕለት ነው፡፡ በሕይወቴ ይሆናል ብዬ ከማላስባቸው ነገሮች አንዱ የሆነውም ትናንት ነው፡፡ አንድ ወዳጄ ማታ ስደውልለት ‹‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቤት ጸሎተ ፍትሐት ልናደርግ መሄዳችን ነው›› አለኝ፤ አላመንኩትም፡፡ ሰዓቱ ከምሽቱ ወደ ሦስት ሰዓት ሆኖ ነበር፡፡ ካህናቱ፣ ዲያቆናቱ፣ መሪጌቶቹ ተሟልተው ሙሉ ጸሎት ሲደረግ ነበር ያደረው፡፡ የቤተ መንግሥቱ ሰዎች ለጸሎቱ የነበራቸው ክብርና ሥነ ሥርዓት የሚገርም ነበር፡፡
ከዚያም የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የመጨረሻውን የጸሎት ሥነ ሥርዓት አሳየን [ግን ጋዜጠኞቹ ምን ነክቷቸው ነው? ሃይማኖታዊ ጸሎት ሲሉ የዋሉት፡፡ ለመሆኑ ሃይማኖታዊ ያልሆነ ጸሎት አለ? ‹ፍትሐት› የሚለው ቃል ጠፍቷቸው ነው? የቻይናው ቴሌቭዥን እንኳን ያወቀውን ቃል እነርሱ ምነው ጠፋቸው? ይባስ ብለው በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የነበረውን ጸሎት ‹ቅዳሴ› እያሉ ይጠሩት ነበር፡፡ ለነገሩማ ‹በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል› ለማለት ‹በቅድስት ካቴድራል ሥላሴ› ይሉ እንደነበር ስሰማ ይቅር ብያቸዋለሁ፡፡ ኧረ እንዲያውም የዛሬው ልቅሶ የሚያምር ልቅሶ ነው ያለን ጋዜጠኛም ነበር፡፡
 ሚዲያዎቻችን ከልምድ ማነስም ሊሆን ይችላ የችግርንና የኀዘንን ወቅት እንዴት መዘገብ እንደሚቻል መማር አለባቸው፡፡ ሁለት ሳምንት ሙሉ የፍቅር እስከ መቃብርን ዋሽንት ብቻ ከማሰማት የተለያዩ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት አይቻልም ነበር? ስለ አቶ መለስ ማንነት የሚያውቋቸውን ማነጋገር፤ የውይይት መርሐ ግብር ማዘጋጀት፤ ሌላም ሌላም አይቻልም ነበር? የቃለ መጠይቅ ጥያቅዎቹስ ለሕፃኑም፣ ለዐዋቂውም፣ ለተማረውም፣ ለማይሙም አንድዓይነት መሆን አለባቸው? ራሳቸው ጋዜጠኛ ራሳቸው ተንታኝ እንዲሆኑስ የቱ አሠራር ነው የፈቀደው? አንዳንዴ እንዲያውም  ስብከትም ሁሉ ይመስል ነበር? ደግሞስ ሰው አኳሽቶና አጋንኖ የሚናገረውን ነገር ሁሉ ማቅረብ አለባችሁ? ጋዜጠኞቻችንኮ ስለ አቶ መለስ ሁሉን ዐዋቂ ሆኑብን፤ ቢያንስ አብረዋቸው የተጓዙት፤ አብረዋቸው የሠሩት፤ አብረዋቸው የኖሩት፤ ስለ እርሳቸው የጻፉት ቀርበው ቢነግሩን ምናለ? ይቺ አሠራር ታስመርራለችና መታረም አለባት]፡፡
ወደ መስቀል አደባባይ የተጓዘውም ከፊትና ከኋላ ድባብ በያዙ ካህናት፣ ማዕጠንት በያዙም ጳጳሳት ታጅቦ ነበር፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝና ካለፈው ጊዜ ይልቅ የፓትርያርኩ ቀብር የመሰለን ይኼኛው ነው፡፡ የጉዞው ሥነ ሥርዓት አዘጋጆቹንም ሆነ አከናዋኞቹን ያስመሰገነ ነበር፡፡ እመለስበታለሁ፡፡
በመስቀል አደባባይ መርሐ ግብሩ በጸሎት መጀመሩን ሳይ ዓይኔ ነው ወይስ ቴሌቭዥኑ ነው? አሰኝቶኛል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደረገ ማነው? የአቶ መለስ ኑዛዜ? የወይዘሮ አዜብ ፍላጎት? ወይስ የመንግሥት ፈቃድ? ከወሬ ባለፈ መረጃ ባውቀው እንዴት በወደድኩ፡፡ መቼም ሰው ሆኖ ከሥላሴ ቤት የሚቀር የለምና የአቶ መለስ አስከሬን ወደ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ የነበረውን ሥነ ሥርዓት ምነው ከሳምንት በፊት ልናየው አልቻልንም አሰኝቶኛል፡፡
አስከሬኑ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ቤተ መቅደሱን ዞሮ ነው ወደ መቃብሩ የገባው፡፡ ባለፈው ጊዜ ይህንን አላየሁምሳ? የካህናቱ ወረብ፣ የሰንበት ተማሪዎቹ መዝሙር፣ የአቡነ ናትናኤልና የአቡነ አረጋዊ ትምህርት ‹‹እውነት ለአቶ መለስ ነው ይህ የሚደረገው?›› አስብሎኛል፡፡ መለስ ከሕይወታቸው ይልቅ[በሕይወታቸው የሠሩትን እንዲህ በሚታይና በሚሰማ ደረጃ ስለማላውቅ] በሞታቸው ቤተ ክርስቲያንን ከፍ ከፍ አድርገዋታል፡፡
ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል ክብርና ሞገስ እንደምትሆን ተተኪዎችም ትምህርት ይወስዳሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
መሪ በመፈንቅለ መንግሥት ሳይገለበጥ፤ በጦርነት ተሸንፎ አገር ጥሎ ሳይወጣ፤ በአብዮት ከዙፋን ወርዶ እሥር ቤት ሳይገባ በተፈጥሮ ሞቶ በክብር ሲቀበር ለእኔ ትውልድ አዲስ ታሪክ ነው፡፡ የኔ ትውልድ ስለ መሪው ስደትና ሞት ሲሰማ እንጂ መሪውን አልቅሶ ሲቀብር አላየሁም፡፡ መለስ በዚህ ታሪክ ሠርተዋል፡፡
ከቤተ መንግሥት እስከ መስቀል አደባባይ፤ ከመስቀል አደባባይ እስከ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የነበረው ሥነ ሥርዓት አዘጋጆቹንም፣ ተሳታፊዎቹንም የሚያስመሰግን ነበር፡፡ የፕሮግራሙ በተያዘለት ሰዓት ማለቅ፡፡ በተለይም አቶ ኩማ ሚደቅሳ እንኳንም መድረኩን ለ‹‹አርቲስቶች›› አልሰጡብን ብያቸዋለሁ፡፡ እንዲህ እጥር ምጥን አድርገው አይመሩልንም ነበር፡፡ [በዚሁ ግን አንድ አስመራ ነገር መናገር ያስፈልጋል፡፡ ሰሞኑን ይወጡ የነበሩ ግጥሞች ከታገል ሰይፉ ግጥም በቀር ሚዛን የሚደፋ አጣሁ፡፡ ትትትትትት፣ንንንንንን፣ ችችችችችች፣ ምምምምምም ብቻ የተደረደረባቸው ናቸው፡፡ አንባቢዎችም ለመድረኩ የማይመጥኑ፣ ግጥሙንም ወደ ስድንባብ በመቀየር የተካኑ ናቸው፡፡ ከተዘፈኑትም መካከል ከአንዱ በቀር የግጥም ለዛ ያለው የለም፡፡ ምነው ለቸበር ቻቻ እንጂ ለኀዘን የሚሆን ግጥም አጣንሳ]
ያ እንደ ደዶፍ የወረደው ዝናብ ሥነ ሥርዓቱን ሳያሰናክለው፡፡ ከፖሊሶቹና ከወታደሮቹ ቆብ ላይ ዝናቡ እንደ ጣራ ፍሳሽ እየወረደ ሥነ ሥርዓቱ ግን ቀጠለ፡፡ መንገዱ ሁሉ ጎርፍ ነበረ፡፡ ተጓዦቹ ግን ችግሩ ሳይፈታቸው እነርሱም ጨዋነታቸውን አሳይተዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያኑ የነበረው ሥነ ሥርዓትም በተያዘው ሰዓት የተከናወነና ለዓይን የማይጎረብጥ ነበር፡፡ አቶ መለስ ተነሥተው የሰሞኑን ሁኔታ ቢያዩ በአንዳንዱ ነገር የሚገረሙና የሚደነቁ፤ በአንዳንዱ ነገር የሚያዝኑና የሚቆጩ፣ በአንዳንዱም ነገራችን የሚናደዱ ይመስለኛል፡፡
በዚያም ተባለ በዚህ ግን አቶ መለስ በሞታቸው ታሪክ ሠሩ፤ እኛም በሳቸው ሞት ታሪክ አየን፡፡

Jul 28, 2012

New RnB Song Month Of July 2012!!!


Wiz Khalifa ft. Busta Rhymes - Different Cloth (New Music July 2012)


Kid Ink ft. Tyga & Chris Brown - Time Of Your Life (Remix) (New Music July 2012)


ፈረንጅ ነውኮ ( በ ዲ/ንዳንኤል ክብረት)

ፈረንጅ ነውኮ



ማክሰኞ ሐምሌ 3 ቀን 2004 ዓም የተዘጋውን የኢንተርኔት መሥመር ለማስከፈት እዚህ አያት መንገድ ጉርድ ሾላ ያለው የቴሌኮሙኒኬሽን ቅርንጫፍ ሄድኩላችሁ፡፡ በጠዋቱ ሠልፉ ለጉድ ነው፡፡ ምናለ የቀበሌ መስተዳድሮች ለአንዳንድ መሥሪያ ቤቶች ሥልጠና ቢሰጡ? ቀበሌ እንኳን የጠፋው ሰልፍ እዚህ ከነ ሙሉ ክብሩ ይንጎማለላል፡፡ አዛውንትና አሮጊቶች እግራቸው እየተንቀጠቀጠ ውጭ በብርድ ቆመዋል፡፡ ያውም ከሠላሳ ደቂቃ በላይ፡፡
እንደምንም ተራ ደርሶኝ ወደ ውስጥ ገባሁ፡፡ እዚያም ለካስ ሌላ ሰልፍ አለ፡፡ ደግነቱ እዚህ የምትሰ ለፉት ተቀምጣችሁ ነው፡፡ ፊት ለፊታችን የተገተሩት ኮምፒውተሮች ብዙዎች ናቸው፡፡ የሚሠሩት ሰዎች ግን ሦስት ኮምፒውተር ለአንድ ሠተራኛ እንዲደርሳቸው ሆነው ነው፡፡ አሁን እነዚህ ሁሉ ኮምፒውተሮች የሚሠራባቸው ከሌለ ለምን ተገዙ? ከተገዙስ ለምን አይሠሩም? ማን መልስ ይሰጣችኋል? ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ አለ ያገሬ ሰው፡፡

 እኛ ካሁን ካሁን ደረሰን እያልን ማርያም ማርያም ስንል አንድ ሕንድ ቦርሳውን አንጠልጥሎ መጣ፡፡ የሚያስተናግዱን ሴትዮ ቀጥ አድርገው ወደ መስተንግዶው ወንበር ወሰዱት፡፡ ይታያችሁ ውጭ አያሌ አዛውንትና አሮጊቶች ቆመዋል፡፡ ውስጥ እኛ ተቀምጠናል፡፡ አላስቻለኝምና ሰውዬውን ተራ እንዲይዝ በሚያውቀው ቋንቋ ነገርኩት፡፡ ወዲያው አስተ ናጋጇ «ተወው» አሉኝ፡፡ ገርሞኝ ወደ እርሳቸው ሄድኩና «ለምን ስል ጠየቅኳቸው፡፡ «ፈረንጅኮ ነው» ብለውኝ እርፍ፡፡
ይሄኔ አዝኜም ተናድጄም «እና ፈረንጅ ቢሆንስ፤ ፈረንጅ አይሰለፍም? ተራ አይጠብቅም? መመሪያችሁ ያዝዛል ደረደርኩት ጥያቄዬን፡፡ ምንም አልመሰላቸውም፡፡ «አንድ ሰው ነው ቢገባ ምናለ» አሉኝ «እዚህኮ በቡድን የመጣ የለም፡፡ ሁላችንም አንዳንድ ሰዎች ነን፡፡ እንደዚህ ለሰው ካሰባችሁ ለምን እዚያ ወገባቸው የሚንቀጠቀጠውን አሮጊቶችና አዛውንት አታስቀድሟቸውም» አልኳቸው፡፡ «እነርሱማ የኛው ናቸው እርሱ ግን ፈረንጅ ነው»
ይኛን ጭቅጭቅ ሰምተው የቦታው ኃላፊ ይመስሉኛል ሌላ ሴትዮ መጡ፡፡ «ምን ሆናችሁ ነው አሉን፡፡ ነገርኳቸው፡፡ «አይዞህ ይደርስሃል፤ አትጨቃጨቅ፡፡ ምናለ አንድ ሰው ነው፡፡» ማለሳለሳቸው ነው፡፡ ሌላም ሰውዬ «አንድ ሰው ነው ማለት ምን ማለት ነው? እኛስ ስንት ሰው ነን ሲል ሁላ ችንም ሳቅን፡፡ ሌላ ተስተናጋጅም «ቅድም እኒያ አሮጊት በምርኩዝ መጥተው አላስገባም አላላችሁም? እኛ አይደለን ይግቡ ግዴለም ብለን ያስገባናቸው? እርሳቸው ለሀገራቸው ሠርተዋል፤ ልጆች አሳድገዋል፤ በእድሜም አርጅተዋል፤ ለእርሳቸው ሳታዝኑ እንዴት ለሕንዱ አዘናችሁለት ሴትዮዋ ነገሩ መክረሩን ሲያውቁ፡፡
«በቃ ተውት፤ ምናልባት ተራ ያዝ ለማለት ቋንቋውስ ከየት ይመጣል ብላችሁ ነው» ብለው ሁላችንንም አሳቁን፡፡
እኛም «ምናልባት ቴሌ ኮሙኒኬሽን ኢትዮ ቴሌኮም ተብሎ ፈረንጆቹ (ፈረንሳውያን) አስተዳደሩን ስለ ያዙት ለፈረንጅ ቅድሚያ እንዲሰጥ ታዝዞ ይሆናል እያልን ወረፋችንን ይዘን ትንታኔያችንን ቀጠልን፡፡
አንዳንድ ወረፋ ያዦች ብዙ ቦታ ሲሄዱ ፈረንጅ ሲፈተሽ እንደማያዩ ተናገሩ፡፡ ሌሎችም በቤተ ክርስ ቲያን ከፈረንጅ ጋር ለሚጋቡት የተለየ ክብር እንደሚሰጥ፣ ለሌላው የማይደረግ የቀኖና ማስተካከያ እንደ ሚደረግ ያጋጠማቸውን አወጉን፡፡ ሌሎችም በየፋብሪካውና በየግንባታ ኩባንያው በስመ ፈረንጅ የመጡ ነጮች ሠራተኛውን ሲደበድቡና ሲበዘብዙ ፈረንጅ በመሆናቸው ብቻ ሃይ የሚላቸው እንደሌለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ በአካባቢው ለሚገኙ የመስተዳድር አካላት ሲያመለክቱም ከአበሾቹ ይልቅ ፈረንጆቹን መስማት እንደ ሚመርጡ ይተርኩ ጀመር፡፡
ይሄኔ ነው የኦፕራ ገጠመኝ ትዝ ያለኝ፡፡ ከተወሰኑ ዓመታት በፊት ታዋቂዋ የቴሌቭዥን መርሐ ግብር አዘጋጅ ኦፕራ ዊንፍሬ ኢትዮጵያ በመጣች ጊዜ ያጠማትን ነገር ኀዘን በተሞላበት ሁኔታ የገለጠችበትን ዝግጅት አቅርባ ነበር፡፡ እርሷ ወደ ኢትዮጵያ ስትመጣ አራት ጠባቂዎችን ቀጥራ ነበር፡፡ ችግሩ ቀጣሪዋ ኦፕራ ጥቁር፣ ተቀጣሪዎቹ ደግሞ ነጮች ሆኑ፡፡ ኢትዮጵያ ደርሳ ከአውሮፕላን ማረፊያው ጀምሮ ኦፕራ ያላገኘችውን ክብርና መስተንግዶ እርሷ የቀጠረቻቸው ነጭ ጠባቂዎቿ እንዴት ያገኙት እንደነበር በኀዘን ገልጣ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነጻነት አምባ ትባላለች እንጂ ራስዋን እንደ ጥቁር አፍሪካ አካል አድርጋ አትመለከትም የሚል ትችትም ሠንዝራ ነበር፡፡
አንዲት አፍሪካውያን በሚበዙበት ድርጅት የምትሠራ ወዳጄ አብራት ለምትሠራው አፍሪካዊት እኅቷ የቤት ሠራተኛ ታፈላልግላታለች፡፡ የቤት ሠራተኛዋ የቀጣሪዋን የሥራ ቦታ ስታውቅ ደሞዙን ሞቅ አደረገችው፡፡ ያችም የሰው ሀገር ሰው አማራጭ ስላልነበራት ተስማማች፡፡ ሥራ የምትጀምርበትን ቀን ቆረጠና የኔ ወዳጅ የቤት ሠራተኛዋን ይዛ ወደ ቀጣሪዋ ቤት ሄደች፡፡
እዚያ ስትደርስ የቤት ሠራተኛዋ ሃሳቧን ቀየረች፡፡ «ቤቱ ሩቅ ነው፤ ትልቅ ነው» የሚሉ የእናቴ መቀነት አደናቀፈኝ ዓይነት ምክንያት መደርደር ጀመረች፡፡ ብትባል ብትሠራ አልነካውም አለች፡፡ በነገሩ አዝ ነው ቀጣሪዋና አስቀጣሪዋ ተሰነባበቱና አስቀጣሪዋ ያችን የቤት ሠራተኛ በመኪናዋ ይዛት ወጣች፡፡
መንገድ ላይ «ከተስማማሽ በኋላ ሃሳብሽን እንዴት ትቀይሪያለሽ? ለምን መጀመርያ አልነገርሽኝም ነበር» አለቻት አስቀጣሪዋ፡፡ የቤት ሠራተኛዋም «እኔ ፈረንጅ መስላኝ ነበር እንጂ» ስትል አስቀጣሪዋ በንዴት መኪናዋን አቆመችና «አንቺ ከደመወዝሽና ከሥራው እንጂ ከሴትዮዋ ቅጣትና ጥቁረት ምን አለሽ አለቻት፡፡ «እንዴ እኔ ጥቁር ቤት እሠራለሁ ማለት አፍራለሁ» ብላት ዕርፍ፡፡ እንግዲህ እርሷ ነጭ መሆንዋ ነው፡፡
አንዱ ችግራችን ራሳችንን የጥቁር አፍሪካ አካል አድረገን አለማየታችን ይመስለኛል፡፡ ስለሌሎች አፍሪካ ውያን ስናወራ እንኳን «ጥቁሮች» እያልን ነው፡፡ የመንግሥቱ ለማ ባሻ አሸብር እንደሆኑት ማለት ነው፡፡ ጥቁርነታችንን አለመቀበላችን ለነጭ የተለየ ቦታ እንድንሰጥ አድርጎናል፡፡ በተለይ ደግሞ ኢትዮ ጵያውያን ወደ ውጭ ሀገር እየሄድን ለመኖር የተለየ ጉጉት ካደረብን ካለፉት ዐርባና ሠላሳ ዓመታት ወዲህ ከፈረንጅ ጋር መሥራት፣ ፈረንጅ ሀገር መሄድ፣ በፈረንጅ ቋንቋ መናገር፣ የፈረንጅ ልብስ መልበስ፣ የፈረንጅ ምግብ መብላት፣ ፈረንጅ ማግባት፣ ፈረንጅ መቅጠር፣ የፈረንጅ ፊልም ማየት፣ የፈረንጅ ስም ማውጣት፣ ፈረንጅ ማስተናገድ፣ የክብርና የደረጃ ማሳያዎች እየሆኑ መጥተዋል፡፡
ዛሬ ዛሬ በሽታ አድጎ አድጎ ተቋሞቻችንና ዩኒቨርሲቲዎቻችን ፈረንጅ መቅጠር፣ በፈረንጅ መመራትና አስተዳደሩን ለፈረንጅ መስጠት የሥልጣኔና የደረጃ መሳያ አድርገውታል፡፡ ሌላው ቀርቶ ይቺ በመዳህ ላይ ያለቺው የፊልም ጥበባችን እንኳን በፈረንጅ ቻይናዎች እየተሞላች መጥታለች፡፡ በሙዚቃ ክሊፖቻችንም ፈረንጅ እስክስታ ሲመታና ሞሰብ ከብቦ እንጀራ ሲመገብ ማሳየት የተወዳጅነቱ ማሳያ ሆኗል፡፡
ስለ አድዋና ማይጨው፣ ስለ ሦስት ዘመን ነጻነትና ስለ ቅኝ አለመገዛት የምናወራው ሁሉ እንደ ላሜ ቦራ ተረት እየሆነ መጥቷል፡፡ በአሜሪካና በአውሮፓ የሚገኙ የኢትዮጵያውያን ምግብ ቤቶች እንኳን ሲፎካከሩ «እዚህ ቤት ነጮች ብቻ ናቸው የሚያዘወትሩት» መባልን የክብራቸው መለኪያ ሲያደርጉት ታያላችሁ፤ ትሰማላችሁም፡፡ ሌላው ቀርቶ ቤተ እምነቶቻችን እንኳን ለሀገሬው ሰዎች አይነኩም አይዳሰሱም የሚባሉትን ነገሮች ለፈረንጆች መፍቀድና ማሳየት ነውር አይመስላቸውም፡፡
ይሄው ለነጮች አልገዛም ብሎ የኖረው መሬት እንኳን ዛሬ ነጭ በነጭ እየሆነ አይደለ፡፡ መሬት ወሰዱ ሲባል የምሰማቸው ሁሉ «ፈረንጆቹ» ናቸው፡፡ መሬት ወሳጆቹም ነጮች፣የሚዘራውም ነጭ፣ የሚሸ ጠውም ለነጭ፡፡
እጅግ በጣም የሚገርመው ደግሞ በተለይ በምዕራብ ሀገሮች ቆይተው የሚመጡ ዳያስጶራ ኢትዮ ጵያውያን ከፈረንጅ ጋር መኖር ያረንጅ ይመስል ራሳቸውን እንደ ፈረንጅ መቁጠራቸው ነው፡፡ አንዳንድ መሥሪያ ቤት ስትሄዱ፣ ወይም አንዳንድ ጉዳይ የሚፈጸምባቸው ቢሮዎች ስትገቡ ዳያስጶራ በመሆናቸው ምክንያት ብቻ ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ይፈልጋሉ፡፡ አንዳንዴማ እነርሱ ከውጭ ስለሚመጡ ብቻ የሊዝ ዋጋ ለእነርሱ እንዲቀንስ፣ መሬት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው፤ መኪናና የቤት ዕቃ ያለ ቀረጥ እንዲ ያስገቡ፣ በየቢሮው የተለየ አስተያየት እንዲደረግላቸው ይጠይቃሉ፡፡ ባለፈው እንኳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በፋሲካ ሰሞን ሰብስቧቸው ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ አንዳችም ነገር ሳያነሡ ለዲያስጶራ ይሄ ይደረግለት፣ ይሄ ይፈቀድለት፣ ይሄ ይሟላለት እያሉ ሲጠይቁ ነው የዋሉት፡፡ ፈረንጆች፡፡
እነርሱ ምን ያድርጉ በኢትዮጵያ ፓስፖርት ለሚገቡ ኢትዮጵያውያን የማይፈቀደው ላፕቶፕ እንኳን በውጭ ሀገር ፓስፖርት ለሚገቡ «ኢትዮጵያውያን» ሲፈቀድ ያያሉ፡፡ አበሻ ከመሆን ይልቅ ፈረንጅ መሆን ሲያስከብር አይተዋል፡፡ ታድያ ቢፈረንጁ ምን ይገርማል፡፡