May 17, 2012

ወሰደው ከፊትዋ



ልጅነት ሆነና ዕረፍት የሌለበት
አንገት ያለሃሳብ የሚመዘዝበት
ልብ ከግንባር ላይ የሚነበብበት
ለጋነት ባጠራው ይሉኝታ ቢስ ፊትዋ
በስልት ያልተገራው ግልጽ አስተያየትዋ
መልሶ ቢያሳየው የራሱን አንካሳ
የባህሉን ጅራፍ የወጉን ጠባሳ
“ምነው ዓይን በላች ይሉኝታ አጣችሳ”“
እያለ ጮኸና ልቧን አስበርግጐ
ወሰደው ከፊትዋ ልጅነትዋን ጠርጐ
በሞረድ ምላሱ ፈግፍጐ ፈግፍጐ . . .

(ታገል ሠይፉ፣ ቀፎውን አትንኩት፣ 1986)

No comments: